በኢትዮጵያ ቡና ቤት ሁለት አመታትን ያክል መጫወት የቻለዉ ሀብታሙ ታደሰ(ቁልጭ) ወደ ሀድያ ሆሳዕና ማምራቱ ተረጋግጧል።
በአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት እየተመሩ ወደ ዝዉዉርር ገበያዉ ጎራ በማለት የተለያዩ አዳዲስ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ የሚገኙት ሀድያ ሆሳዕናዎች አሁን ደግሞ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች የሆነዉን ሀብታሙ ታደሰን ከኢትዮጵያ ቡና ወደ ስብስባቸዉ መቀላቀላቸው ታዉቋል።
የቀድሞዉ የወልቂጤ ከተማ ተጫዋች የዉድድር አመቱን በቡናማዎቹ ቤት ምንም እንኳን ወጥ በሆነ አቋም መጫወት ባይችልም ከቡድን አጋሮቹ አቡበከር ናስር እና ሚኪያስ መኮነን ጋር ጥሩ ጥምረትን በመፍጠር ክለቡ ኢትዮጵያ ቡና በኮንፌዴሬሽን ካፕ እንዲሳተፍ የበኩሉን ድርሻ መወጣት መቻሉ ይታወሳል።
በመጨረሻም አጥቂዉ ሀብታሙ ታደሰ ሁለት አመት በሚቆይ የስምምነት ዉል ለሀድያ ሆሳዕና ለመጫወት ፊርማዉን አኑሯል።


