ለቀጣዩ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እንዲሁም በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ለሚኖራቸው ዉድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነዉ ለመቅረብ ይረዳቸዉ ዘንድ እስከ አሁን ድረስ የአራት ተጫዋቾችን ዝዉዉር ያጠናቀቁት ቡናማዎቹ አሁን ደግሞ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነዉን አቤል እንዳለ ወደ ስብስባቸዉ መቀላቀላቸው ታዉቋል።

ረዘም ላለ አመት ለደደቢት መጫወት የቻለዉ አማካዩ አቤል በተጠናቀቀዉ የዉድድር አመቱ ፈረሰኞቹን ተቀላቅሎ ጥሩ እንቅስቃሴን ማድረጉ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሌላኛዉን የሸገር ክለብ ኢትዮጵያ ቡናን መቀላቀሉ ተረጋግጧል።


