ከአሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ጋር ከተለያዩ በኋላ ረዘም ላለ ጌዜ አዲስ አሰልጣኝ ሳይሾሙ የቆዩት ሰበታዎች ባሳለፍነዉ ሳምንት ዘላለም ሽፈራዉን በዋና አሰልጣኝነት መሾማቸዉ ይታወሳል።
ከአሰልጣኝ ቅጥር በኋላ ወደ ዝዉዉር ገበያዉ በመግባት አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ በመቀላቀል ላይ የሚገኙት ሰበታወች በዛሬዉ ዕለትም አንድ ተጫዋች ሲያስፈርሙ የሶስት ነባር ተጫዋቾቻቸውን ዉልም አራዝመዋል።
የዉድድር አመቱን በአቃቂ ቃሊቲ ያሳለፈዉ ዮናስ አቡሌ ሰበታ ከተማን በሶስት አመት የዉል ስምምነት መቀላቀሉ ተረጋግጧል።
- ማሰታውቂያ -
በተጨማሪም ክለቡ የነባር ተጫዋቾቹን ፍፁም ገ/ማርያም ፤ ሹሬሳ ሹቢሳ እና ናትናኤል ለተጨማሪ አመታት ማራዘሙ ተሰምቷል።
የዉድድር አመቱን በድንቅ ብቃት በመጫዎት እና ጎሎችን በማስቆጠር ያጠናቀቀዉ አጥቂዉ ፍፁም ገ/ማርያም አሁንም ከሰበታ ጋር ተጨማሪ አንድ አመት ለመቆየት ተስማምቷል።
በተጨማሪም በሴካፋ ከ23 አመት በታች ዉድድር ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባል የነበረዉ የመስመር አጥቂዉ ዱሬሳ ሹቢሳ ለተጨማሪ ሶስት አመታት በክለቡ የሚያቆየዉን ዉል የፈረመ ሁለተኛው ተጫዋች ሆኖአል። በተያያዘም የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ናትናኤል ጋንጁላ ተጨማሪ የአንድ አመት ዉል መፈረሙ ተረጋግጧል።


