ፋሲል ከነማ በአሰልጣኙ ዮሀንስ ሳህሌ የዋሊያዎቹ ቅጥር ዙሪያ መረጃ አልነበረኝም ሲል ቅሬታውን አሰማ።
ከክለቡ ውስጥ አዋቂ በተሰማ መረጃ አሰልጣኙ ለዋሊያዎቹ መመረጡን ክለቡ የሰማው በመገናኛ ብዙሀን መሆኑ ቅሬታ እንደፈጠረበት ታውቋል።
ምንጫችን እንደገገለጸው ዋሊያዎቹ እሰከ ሰኔ ድረስ ውድድር ስለሌላቸው አመቱ መጨረሻ ድረስ ፋሲል ከነማን ደርቦ እንዲይዝ ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ በሚጠበቅበት ሰአት መግለጫውን መስማታቸው እንዳሳዘናቸው ታውቋል። ከአመታት በፊት ለኢትዮጵያ መድንና ለአሰልጣኝ ገብረ መድህን ሃይሌ የተሰጠው ዕድል ፋሲል ከነማ አለማግኘቱም ቅሬታ የፈጠረ ሆኗል
አሰልጣኝ ዮሀንስ በጎንደር 5 ዞን በሚገኙ 9 የታዳጊ ማሰልጠኛ ማዕከልን እየመራ እንደነበርና አመቱን በጥሩ ውድድር እያካሄደ ያለው ፋሲል ከነማ እቅድን ከግምት ሳያስገቡ ፌዴሬሽኑ የሰጠው ሹመት ክለቡን ማበሳጨቱ ከታማነኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
- ማሰታውቂያ -
በሃሙሱ መግለጫ ፋሲል ከነማን በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ አሰልጣኙና ዋና ስራ አስፈጻሚው በለዘብታ ያለፉት ሲሆን ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን በሰጡት ምላሽ አሰልጣኙ የዋሊያዎቹ አዲሱ አሰልጣኝ ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ አጠር ያለ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተፈጠረው ቅሬታ ዙሪያ ፋሲል ከነማ በቅርቡ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።


