“እንደወንዶች አሰልጣኞች ብዙ ክብር ባይሰጠኝም ሴቶችን በማሰልጠኔ ኩራት ይሰማኛል”
አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው
የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ የሴቶች ቡድን አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው በ26 የአሰልጣኝነት ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ 25 ጨዋታ ሳይሸነፍ የዘንድሮውን ዋንጫ ማሸነፉን አረጋገጠ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሴቶች ቦሌም ክፍለ ከተማን 5ለ0 በማሸነፍ በተከታታይ አምስት አመታት ዋንጫ ማንሳቱን አረጋግጧል።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዘንድሮው የውድድር አመት በ25 ጨዋታ 18ምቱን አሸንፈው 7ቱን አቻ ተለያይተው አንድ ቀሪ ጨዋታ እየቀራቸው በ61 ነጥብ የሊጉ ልዕለ ሃያል መሆናቸውን አረጋገጠዋል።
- ማሰታውቂያ -
አሰልጣኙ ብርሃኑ ግዛው በ26 የአሰልጣኝነት ታሪኩ 27 ዋንጫ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ደግሞ በ14 አመታት 8ቱ የሊግ ዋንጫን ጨምሮ 16 ዋንጫ ማንሳቱንም አረጋግጧል።
አሰለጣኙ ከንግድ ባንክ ጋር ሪከርድ በሆነ 50 ጨዋታ ወይም 4550 ደቂቃ ሽንፈት ሳይገጥመው ተጉዟል። በአሰልጣኝነት ህይወቱ ከየካ ክፍለ ከተማ ጋር 2 ፣ ከሴንትራል ጤና ኮሌጅ ጋር 3 ፣ ከአዲስ አበባ ምርጥ ጋር 6 ዋንጫ ሲያነሳ ከነገሰበት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ደግሞ 8 የፕሪሚየር ሊግ በታሪክ በኢትዮጲያ ክለቦች ታሪክ የመጀመሪያ ያደረገውን አንድ የሴካፋ ዋንጫ ፣ 1 የአ/አ አንደኛ ዲቪዚዮን፣ 1 የጥሎ ማለፍ ፣ 2 የአሸናፊዎች አሸናፊ እና 3 ሰሜን ማዕከላዊ ዋንጫውን አንስቷል።
አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው ዋንጫውን ማንሳቱን ካረጋገጠ በኋላ እንደተናገረው ” እንደወንዶች አሰልጣኞች ብዙ ክብር ባይሰጠኝም ሴቶችን በማሰልጠኔ ኩራት ይሰማኛል የማሰልጥናቸው ተጨዋቾቼ እንዲሁም የሚደግፉኝ ጥቂቶችና ከኢትዮጵያዊያን ያገኘሁት ክብር ግን በታሪክ የሚቀመጥ ነው” ሲል ደስታውን ገልጿል።


