By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ” ስንሸልማቸው ስንደግስላቸው የኖሩት ሃይሌና ገዛኧኝ ገንዘብ እየባከነ ነው ሽልማቱ ለፓሪሱ ጀግኖች አይገባቸውም ማለታቸው ያሳዝናል” ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ / የኢት. ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት/
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንአትሌቲክስኦሎምፒክ ኮሚቴ

” ስንሸልማቸው ስንደግስላቸው የኖሩት ሃይሌና ገዛኧኝ ገንዘብ እየባከነ ነው ሽልማቱ ለፓሪሱ ጀግኖች አይገባቸውም ማለታቸው ያሳዝናል” ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ / የኢት. ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 1 year ago
Share
SHARE

” ስንሸልማቸው ስንደግስላቸው የኖሩት ሃይሌና ገዛኧኝ ገንዘብ እየባከነ ነው ሽልማቱ ለፓሪሱ ጀግኖች አይገባቸውም ማለታቸው ያሳዝናል”
ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ
/ የኢት. ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት/

“ወደ ፓሪስ የሄድነው የተቀመጠ ሜዳሊያ ለማምጣት ሳይሆን በውድድር አሸንፈን ለማግኘት ነው”
ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ
// የኢት .አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት /

 

የአቴሌቶችና አሰልጣኞች ችግርን ለማስወገድ ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ የሚገኙበት የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት እንደሚጥር የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አስታወቀ።

- ማሰታውቂያ -

ትላንት ምሽት በማሪዮት ሆቴል በተካሄደው የፓሪስ ኦሎምፒክ አሸናፊ አትሌቶችና አሰልጣኞች በተካሄደ የሽልማትና የዕውቅና ስነስርዓት ላይ የኮሚቴው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ እንደተናገሩት እየተንከባለለ የመጣውን ችግር መንግስት የማስወገድ ሙሉ ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል።

” ክቡር ጠ/ሚ ባሉበት የአትሌቶችና የየአሰልጣኞችን ችግር እንዲያዳምጡ ችግሩም እንዲፈታ ለማድረግ የምንችለውን እናደርጋለን አይዟችሁ መንግስት ከጎናችሁ ሆኖ ሁሉን ችግሮ ይፈታል ብለን እናምናለለን ኢትዮጵያን ከችግር ለማውጣት ተነሱ የናንተ ጥቅም ሁለተኛ ጉዳይ ነው” ያሉት ፕሬዝዳንቱ ” ለግለሰቦች መስጠት ቢቸግረንም አትሌቶችና አሰልጣኞች በጋራ ሆነው ከመጡ ውጪ ያገኙትን ገንዘብ ኢንቨስት ማድረግ ከፈለጉ ቦታ እንሰጣለን ብለው ቃል ገብተዋል ለዚህም ለክቡር ጠ/ሚ ከፍ ያለ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል” በማለት ተናግረዋል።

የኦሎምፒክ ኮሚቴ እንደገና በይግባኝ መታገዱን ተገቢ ያልሆነ ድርጊት ነው ያሉት ዶክተር አሸብር ”
ስንሸልማቸው ስንደግስላቸው የኖርነው
ጀግኖች አትሌቶቻችን ሃይሌና ገዛኧኝ ለፓሪስ ጀግኖች አትሌቶችና አሰልጣኞች ሽልማት በምንሰጥበት ሰአት ገንዘብ እየባከነ ነው ሽልማት አይገባቸውም በሚል አካውንቱን እንደገና አሳግደውታል በተለይ ሃይሌ ከመሰለ ሲሸለም ከኖረ አትሌት ይሄ ድርጊት መፈጸሙ አይገባም እነሱ ሲያሳግዱ እኛ ስናስነሳ ቆይተናል አሁንም በዚህ ደረጄ አይቸግርም እንወጣዋለን ካለማወቅ የሚመጡ ቀላል ፈተናዎችን እንወጣለን ቲማችን ጠንካራ ነው አዲሱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስራ ከጀመረበት ከነሀሴ 13 ጀምሮ ደራርቱና ህይወት ከመጨመራቸው ውጪ ሁሉም በጋራ የሚሰራ የሚተዋወቅ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

ስለ ፓሪስ ኦሎምፒክ ደከም ያለ ውጤት የተናገሩት ዶክተር አሸብር የተለመደው ውጤት ከራቀን ቆይቷል በፓሪስ ህዝቡ የጠበቀውን አላገኘም ብሄራዊ ቡድኑ ከተበተነና ግሎባል ማርኬቱ ኢትዮጵያም ሆነ አለም ላይ ተጽዕኖ መፍጠር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ እየወረደ ነው ለተሻለ ድል የተሻለ ጠንካራ ስራ ያስፈልገዋል” ሲሉ አስረድተዋል።

” ዛሬ ለሽልማት እንደተገናኘን በቀጣየይ ስለ ፓሪስ ኦሎምፒክ ጠንካራ ደካማ ጎን ለመምከር ውይይት ተዘጋጅቷል ተገናኝተን ችግሮቻችን ለይተን አውቀን ፈተናዎቻትንን አውቀን ወደፊት የምንጓዝበትን መንገድ መፈጠር አለበት” ያሉት ፕሬዝዳንቱ “እንደ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ስለ ፓሪስ እያሰብን አይደለም አሁን የምናስበው ስለ ሎስ አንጀለስ ኦሎምፒክ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ዶክተር አሸብር ለተሸላሚዎቹ እንደገለጹት የዛሬ ማበረታቻ እናንተን የሚመጥን አይደለም ገንዘቡ ሳይሆን ዋናው ክብሩ ነውና ሽልማቱ እንደምናስባችሁ እንደምናስታውሳችሁ ለመግለጽ ነው” ሲሉ አስተያታቸውን ሰጥተዋል።

በዚሁ የማሪዮት ሆቴል መርሃግብር ላይ የኦሎምፒክ ኮሚቴው ም/ል ፕሬዝዳንትና የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በበኩሏ “ወደ ፓሪስ የሄድነው የተቀመጠ ሜዳሊያ ለማምጣት ሳይሆን በውድድር አሸንፈን ለማግኘት ነው” ስትል ተናግራለች።

” ውጤት ለማምጣት የተቻላችሁን አድርጋቾኋል ነገር ግን ያሰብነው አልመጣም በፓሪስ ኦሎምፒክ ውጤት ለማምጣት በየፊናችን የምንችለውን አድርገናል ነገር ግን አልተሳካም ነገም ሌላ ቀን ነው ውጤቱ ይመጣል እናንተን አደራ የምለው ስነልቡናችሁን ጠብቁ ዋናው እሱ ነው ውጤቱ በቀጣይ ይመጣል ” ስትል ረዳት ኮሚሽነሯ ተናግራለች።

“ጀግኖች አትሌቶቻችን ለሀገራቸው ባመጡት ድል ባንዲራዋን ከፍ አድርገዋል ከአፍሪካም በውጤቷ የተሻለ ሀገር አድርገዋታል.. ለነሱ ክብር ሁሉ ይገባቸዋል ” ያለችው ምክትል ፕሬዝዳንቷ ” የፓሪስ ኦሎምፒክ አልፏል በውድድሩ ያሸነፋችሁ እንኳን ደስ አሊችሁ ያልተሳካላችሁ ደግሞ ነገም ጊዜ አላችሁ አይዟችሁ” ስትል አበረታታለች።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አካውንት በድጋሚ በይግባኝ ታገደ….
Next Article የመቻል ስፖርት ክለብ የግብ ጠባቂ አሰልጣኞች ስልጠና ሊሰጥ ነው….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ

“ወልዋሎን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳለፋችን፤ ከመቀሌ ከተማም በላይ ሆነን በመቀመጣችን ተደስተናል”አላማንታ (ማሪዮ)

Mussie Girmay By Mussie Girmay 9 years ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልምምዳቸውን ቀጥለዋል !
ባህርዳር ከተማ የመስመር ተከላካይ አስፈርሟል
ሀትሪክን በነገው እትም የሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል
የጨዋታ ቅድመ – እይታ | ሀዋሳ ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
Welcome Back!

Sign in to your account

Lost your password?