በ26 ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ የመጨረሻው የሳምንቱ ጨዋታ ዛሬ በ10 ሰአት በአዲስ አበባ ሲታዲየም የተደረገው የሊጉ መሪ ቅ/ጊዮርጊስ እና የሃዋሳ ከተማ ጨዋታ በቅ/ጊዮርጊስ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ሁለቱ ክለቦች የተመጣጠነ የኳስ ፍሰት የነበረው ጨዋታ ሲጫወቱ ነበር ገና ጨዋታው በተጀመረ በ4ኛው ደቂቃ የሃዋሳው አጥቂ ጋዲሳ መብራቴ በግራ በኩል አጥብቦ የመታትን የግቡ ቋሚ መልሶበት ግብ ሳይሆን ቀርቷል ሃዋሳ ከተማዎች ሌላ የግብ ማግባት አጋጣሚ ለመፍጠር 20ደቂቃ መጠበቅ ነበረባቸው በ24ኛውደቂቃ ጋዲሳ መብራቱ ከፍሬው ሰለሞን የተቀበለውን ኳስ ወደ ግብ ሞክሮ የፈረሰኞቹ ግብ ጠባቂ ዘሪሁን መልሶበታል። ቅ/ጊዮርጊስ በበኩሉ የጨዋታውን አብዛኛውን ደቂቃ በራሳቸው ሜዳ ላይ ኳስን ተቆጣጥሮ ለመጫወት ነበር የሞከሩት አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት የግብ እድሎችን ለመፍጠር ሲሞክሩ ተስተውለዋል ገና ጨዋታው በተጀመረ በ5ኛው ደቂቃ ሳላዲን ሰኢድ ከበረኛ ጋር ተገናኝቶ መጠቀም ያልቻለበት እንዲሁም በ13ኛው ደቂቃ የግቡ አግዳሚ መልሶ ያወጣበት ለፈረሰኞቹ የሚያስቆጭ አጋጣሚ ነበር ሆኖም በ16ኛው ደቂቃ ከኒክማ የተሻገረለትን ኳስ የተከላካዮች ስህተት ተጠቅሞ ሳላዲን በቀላሉ በረኛውን በማለፍ የጨዋታውን ብቸኛ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ 3ደቂቃ ሲቀረው ሳላዲን ከሃዋሳው በረኛ ከሳሆሆ ጋር ተገናኝቶ ሳሆሆ የመለሰበት ሌላው ተጠቃሽ የግብ ማግባት ሙከራ ነበር።

በሁለተኛው አጋማሽ የመጀመሪያውን 20ደቂቃዎች የሃዋሳ ከተማ ተጨዋቾች ኳስን ተቆጣጥረው የተሻለ ተንቀሳቅሰው ነበር ነገርግን ምንም አይነት የግብ ማግባት ሙከራ የታከለበት አልነበረም ከ67ኛው ደቂቃ ቡሃላ ግን ፈረሰኞቹ አዳነ ግርማን በራምኬል ሎክ ፍሬዘር ካሳን በደጉ ደበበ እንዲሁም ምንተስኖት አዳነን በተስፋዬ አለባቸው ከቀየሩ ቡሃላ ጨዋታውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ችለዋል ሃዋሳ ከተማዎች መድሃኔ ታደሰ እና ፍርዳወቅ ሲሳይን ወደሜዳ ቀይረው ቢያስገቡም ውጤቱን መቀልበስ ግን አልቻሉም። በዚህም ቅ/ጊዮርጊስ መሪነቱን ሲያጠናክር ከተከታዩ ሲዳማ ቡና አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው ልዩነቱን በ3 ነጥብ አድርሷል።
አስተያየት ይስጡ