መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረሰኞቹ ዩጋንዳ ኢንቴቤ አየር መንገድ ደርሰዋል
ቅዱስ ጊዮርጊስአፍሪካአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ

ፈረሰኞቹ ዩጋንዳ ኢንቴቤ አየር መንገድ ደርሰዋል

አጋራ
አጋራ

 

በ2018ቱ የቶታል ካፍ ሻምፒዬንስ ሊግ እየተሳተፉ የሚገኙት ፈረሰኞቹ በመጀመሪያው ዙር የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የሱዳኑን አልሰላም ዋኡ በፎርፌ በማሸነፍ ከዩጋንዳው ካምፓላ ሲቲ (ኬሲሲኤ) ጋር መገናየታቸው ይታወቃል፡፡

ፈረሰኞቹ ተጋጣሚያቸውን ካምፓላ ሲቲ (ኬሲሲኤ) ባለፈው ሳምንት በሜዳቸው አዲስ አበባ ስታዲዬም በገጠሙበት ጨዋታ ያለ ግብ መለያየታቸው የሚታወስ ሲሆን የመልሱን ጨዋታ ለማድረግ ዛሬ ረፋድ 4:05 ከቦሌ አየር መንገድ ወደ ዩጋንዳ ኢንቴቤ አየር መንገድ ያመሩ ሲሆን ከደቂቃዎች በፊት መድረሳቸው ታውቋል፡፡

የፈረሰኞቹ ልዑካን ቡድን ኤንቴቤ አየር መንገድ ሲደርስ በርካታ ዩጋንዳዊያን ለግብ ጠባቂው ሮበርት ኦዶንካራ አቀባበል ከማድረጋቸውም ባሻገር የሬድዮና የቴሌቪዥን ባለሙያዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል፡፡

በፈረሰኞቹ ልዑካን ቡድን ስብስብ በጉዳት ምክንያት የፊት መስመሩ ንጉስ ሳላዲን ሰይድ አለመጓዙ ተነግሯል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ፈረሰኞቹ ከኢንቴቤ አየር መንገድ፡ተነስተው ጨዋታው ወደሚደረግበት ወደ ዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ እያመሩ ነው፡፡

የዩጋንዳ የቀኑ የአየር ሁኔታ ከፊል ዝናባማ እና ጭጋጋማ መሆኑን የሜትሮሎጂ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

photo credit-st george page

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በቢጂአይ ኢትዮጵያ ስፖንሰር ሊደረግ ነው

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀድሞው አጋሩ ጋር በድጋሚ ለመጣመር ውይይት አድርጓል። አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስን...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቅዱስ ጊዮርጊስ የቀድሞው ተጫዋቾች ማህበር አቋቋሙ

የቅዱስ ጊዮርጊስን ችግር ለመቅረፍ ያለመ በቀድሞው ተጫዋቾች የተሰየመ ማህበር በዛሬው ዕለት በይፋ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የሽግግር ኮሚቴ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ መረጠ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ካጋጠመው ውስጣዊ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተቋቋመው የሽግግር ኮሚቴ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የፈረሰኞቹ የሰላም ውይይት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል…..

... ከሳሹ ወገን ዛሬ ቦርዱ ሃላፊነቱን መልቀቁን በይፋ ማሳወቅ አለበት እያለ ነው...