የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ 42ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ዛሬ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።
በጉባኤው 12 ዋና ዋና አጀንዳዎች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የ2016 የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦም ምክክር ተደርጎበታል።
በጉባኤው የፋይናንስ እና ኦዲት ሪፖርት ተመርምሮ ፀድቋል።
የቀጣይ አራት አመታት ስትራቴጂካዊ እቅድ መፅደቁም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴን ለቀጣዮቹ አራት አመታት ለመምራት ብቸኛ እጩ ሆነው የቀረቡት የቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ የኮሚቴው ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ዶክተር አሸብር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው ይታወሳል።
አስተያየት ይስጡ