በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 4ኛ ሳምንት በምድብ-ለ ደቡብ፡ፖሊስ ከ ናሽናል ሲሜንት አገናኝቶ ባለሜዳዎቹ ደቡብ ፓሊሶች በሰፊ የጎል ብልጫ 6-0 በሆነ ውጤት ናሽናል ሲሜንትን መረምረም ችልዋል።
በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ኳስን ተቋጣጥሮ በመጫወት ባለሜዳዎቹ ደቡብ ፖሊሶች ብልጫ ነበራቸው፡፡ በ4ተኛ ደቂቃ አገኘው ለኪሳ ላይ የተሰራውን ጥፋት ተከትሎ የተሰጠውን ፍ.ቅ.ም እራሱ አገኘው አስቆጥሮ የማህል ዳኛው ሽሮታል።13ተኛ ደቂቃ ከአኘው የተቀቀለውን ኳስ ብሩክ ኤልሊያስ ወደ ግብ ቀይሯታል።በኳስ በቁጥጥር እንግዳዎቹ የተሻሉ ነበሩ። ወደ ግብ ጋር በመድረስ እና ሙከራ በማድረጉ ደቡብ ፓሊስ ጥሩ ነበር።ብሩክ ኤሊያስ,ኤሪክ ሙራንዳ እና አገኘው በተደጋጋ ሙከራ በማድረግ ጫና ፈጥረዋል በ44 በደቂቃ ኤሪክ ሙራንዳ ፍፁም ቅጣት ምት ጎል 2ለ0 እረፍት ወጥተዋል። በሁለተኛው አጋማሽ ደቡብ ፓሊስ በኳስ ቁጥጥሩ ተሻለው ነበር በተለይም ቢኒያም አድማሱ ጥሩ ሲንቀሳቀስ ነበር።

በጫወታው ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው ብሩክ ኤሊያስ የግል ብቃቱን ተጠቅሞ በ70ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል ወዲያው በመልሶ ማጥቃት ከኤሪክ ሙራንዳ የተሻገረለትን አገኘው ሊኪሳን ቀይቆ የገባው አበባው ዮሐንስ ግብ እስቆጥሮ 4ለ0 አድርጎታል።በ82 በደቂቃ ሙዲን አብደላ እንዲሁም ኤሪክ ሙራንዳን ቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው በሀይሉ ወገኔ በ89ኛው ደቂቃ ግብ አስቆጥሮ 6ለ0 በሆነ ውጤት ጫዋታው ተጠናቋል።
ደቡብ ፖሊስ በ3 ጨዋታ 4 ነጥብ በማግኘት 3ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል
የአሰልጣኞች አስተያየት
ደቡብ ፓሊስ- አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ
ያገኘናቸውን እድሎች መጠቀማችን ጨዋታውን ተቆጣጥረን ግቦችን አስችናል።በእራሳችን ክፍተተት ያጣናቸው ነጥቦች ነበሩ አሁን ወደ አሸናፊነት ተመልሰናል በቀጣይ በሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪእንሆናለን።
ናሽናል ሴሜንት – አሰልጣኝ ፍቅሩ ተዘራ
በመጀመርያ አጋማሽ ኳስ ይዞ በመጫወት ጥሩ ነበርን ነገር ግን ግብ በማግባቱ የተሻሉ ነበሩ ምንም ማረግ አልቻልንም ተጫዋቾቹቼ ሜዳው ከብዱቸው ነበር። ባለፉት ጫዋታዎች ጥሩት ነበርን በቀጣይ ወደ አሸናፊነት። እንመለሳለን።
አስተያየት ይስጡ