ለውድ አንባቢዎቿ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን በሚወዱት መልኩ ይዛላችሁ ትቀርባለች፤ የእኛ እና የእርሶ የሆነችው ሀትሪክ ስፖርት ከሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ የምስራቅ አፍሪካን ወክለው የካፍ ስራ አስፈፃሚ ውስጥ ለመግባት ሰፊ እድልን ስለያዙበት ሁኔታ ዘገባዋን ይዛላችሁ ስትቀርብ ሌሎቹ ደግሞ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን መሪነትን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከተረከበው የአዳማ ከተማው ስኬታማ ተጨዋች ሱራፌል ዳኛቸው ጋር በክለቡና በእራሱ አቋም ዙሪያ ስለሰጠው አስተያየት፣ የጅማ አባቡናው አሰልጣኝ ደረጄ በላይም ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ተጫውቶ 1-1 ከተለያየ በኋላ ከክለቡ ጋር ስለተለያየበት እና ስለቡድኑ የሚሰጠው አስተያየት አለ፤ ሌላው የቅዱስ ጊዮርጊሱ ረዳት አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝም ከጅማ አባቡና ጋር ከተጫወቱ በኋላ ስለቡድናቸው የሰጠው አስተያየትም አለ፤ ከባህር ማዶ ዘገባዎች ውስጥ ደግሞ በጋቦን አስተናጋጅነት እየተካሄደ ስላለው የአፍሪካ ዋንጫ፣ የአርሰናል ነፍስ አዳኝ ስለሆነው አሌክሲስ ሳንቼዝ ስለ ማንቸስተር ዩናይትዱ ታሪክ ሰሪ ተጨዋች ዋይን ሩኒ፣ የሊቨርፑል ምልክት ስለሆነው ስቴቨን ጄራርድ በአዲስ የህይወት ምህራፍ ስለመምጣት እና የቼልሲው ዲያጎ ኮስታ ለቡድኑ የውጤታማነት ቁልፍ ሰው ስለመሆኑ ሀትሪክ በሰፊው ልታስኮመኩማችሁ ተዘጋጅታለች፤ ሀትሪክ ስፖርት ከእነዚህ ዘገባዎቿ በተጨማሪ በመዝናኛ አምዷም የምትወዱት ምርጥ ዘገባዎችም ይኖራታልና፤ እንዳታመልጦት፡፡ የሀትሪክ ስፖርት የነገው የፊት ገፅ ይህንን ይመስላል
አስተያየት ይስጡ