መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ2018 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የክለቦች ውድድር የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚዎች ይፋ ሆነዋል።
ቅዱስ ጊዮርጊስአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ

በ2018 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የክለቦች ውድድር የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚዎች ይፋ ሆነዋል።

አጋራ
አጋራ

በ2018 የቶታል ካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎች ይፋ ሲሆኑ ኢትዮጵያን ወክሎ የሚወዳደረው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከደቡብ ሱዳኑ አል ሰላም ዋኡ ጋር ተደልድሏል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ለዚህ ውድድር የበቃው የ2009 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ እንደሆነ ይታወቃል።

የሻምፒዮንስ ሊጉ ቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከየካቲት 2-4 2010 ዓ·ም ወይም እ.ኤ.አ ከየካቲት 9 – 11 2018 የሚደረጉ ሲሆን የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ ወደ ምድብ ድልድል ለመግባት ቀጣዩ ጨዋታውን ከማዳጋስካሩ ሲኤንኤፒኤስ እና ከዩጋንዳው ኬሲሲኤ አሸናፊ ጋር በ1ኛ ዙር ማጣሪያ ከየካቲት 30 – መጋቢት 2 2010 ዓ·ም ወይም እ.ኤ.አ ከመጋቢት 9 – 11 2018 ድረስ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ ካፍ ድረ ገጽ ላይ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። የ3 ጊዜ የደቡብ ሱዳን የክለቦች ዋንጫን ማሸነፍ የቻለው አል ሰላም ዋኡ ይህ ውድድር በታሪኩ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሻምዮንስ ሊግ ጨዋታው ነው። ይህ ዋኡ በተባለው የደቡብ ሱዳን ግዛት ውስጥ የሚገኘው ክለብ 1200 ሰው የሚያስተናግድ ዋኡ የተባለ ስታዲየም ያለው ክለብ ነው፡፡
የቅድመ ማጣሪያው ሙሉ ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በቢጂአይ ኢትዮጵያ ስፖንሰር ሊደረግ ነው

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከቀድሞው አጋሩ ጋር በድጋሚ ለመጣመር ውይይት አድርጓል። አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስን...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቅዱስ ጊዮርጊስ የቀድሞው ተጫዋቾች ማህበር አቋቋሙ

የቅዱስ ጊዮርጊስን ችግር ለመቅረፍ ያለመ በቀድሞው ተጫዋቾች የተሰየመ ማህበር በዛሬው ዕለት በይፋ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የሽግግር ኮሚቴ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ መረጠ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ካጋጠመው ውስጣዊ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተቋቋመው የሽግግር ኮሚቴ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የፈረሰኞቹ የሰላም ውይይት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል…..

... ከሳሹ ወገን ዛሬ ቦርዱ ሃላፊነቱን መልቀቁን በይፋ ማሳወቅ አለበት እያለ ነው...