መነሻ ገጽ Uncategorized በፕሪሜየር ሊጉ ደደቢት ድል ሲቀናው ኢትዮጵያ ቡና አቻ ወጥቷል
Uncategorized

በፕሪሜየር ሊጉ ደደቢት ድል ሲቀናው ኢትዮጵያ ቡና አቻ ወጥቷል

አጋራ
አጋራ

 

በ27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬም ቀጥሎ ሲካሄድ ደደቢት እና ሀዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል።

ደደቢት በአዲስ አበባ ስታዲየም ፋሲል ከተማን አስተናግዶ 2 ለ 1 አሸንፏል።

ለደደቢት ሁለቱንም ግቦች ጌታነህ ከበደ ሲያስቆጥር ለፋሲል ኤደም ኮድዞ ከመረብ አዋህዷል።

ሀዋሳ ከተማም በተመሳሳይ ወልዲያ ከተማን 2 ለ 1 የረታ ሲሆን፥ ፍሬው ሰለሞን እና ጃኮ አራፋት የማሸነፊያ ጎሎቹን አስቆጥረዋል። ለወልዲያ ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ አንዱአለም ንጉሴ ማስቆጠር ችሏል።

image-0-02-04-9ebb995c04b69e397debcbe4628dd1f89ce97d9c0acfd08efee0e27a0070a86c-V

አርባ ምንጭ ከተማ ከአዳማ ከተማ ያደረጉት ያለው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ ተጠናቋል።

image-0-02-04-3af50b2db4f4c5b8cd5bd30674f081f7d3d82f1763f8f66ae9685e184e977b32-V

በሊጉ 12ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ተጫውቶ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ተክሉ ተስፋዬ በ28ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ ቀዳሚ መሆን ቢችልም ሳሙኤል ሳኑሚ በ48ኛው ደቂቃ ኢትዮጵያ ቡናን አቻ አድርጓል።

የ27ኛው ሳምንት መርሃ ግብር የመጨረሻ ጨዋታ ሰኞ አዲስ አበባ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ወላይታ ዲቻን ያስተናግዳል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪነቱን ያጠናከረበትን ድል ጅማ ላይ ተቀዳጅቷል  ዝርዝሩን ይህን ተጭነው ይመልከቱ  

ደረጀ ሰንጠረዥ

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...