የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ዛሬ በሃዋሳ አለም አቀፍ ስታዲየም የቡና ደርቢን አስተናግዷል።

በጨዋታው ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 1 በማሸነፍ መሪነቱን ከቅዱስ ጊዮርጊስ መረከብ ችሏል።
ሲዳማ ቡናዎች በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ባስቆጠሩት ጎል መምራት ሲችሉ፥ ኢትዮጵያ ቡናዎች ደግሞ ለእረፍት ሲቃረቡ ባስቆጠሩት ጎል አቻ መሆን ችለው ነበር።
ከእረፍት መልስ ሲዳማ ቡናዎች ባስቆጠሯቸው ሁለት ጎሎች ጨዋታውን 3 ለ 1 ማሸነፍ ችለዋል።
በዚህም ሲዳማ ቡና የፕሪሚየር ሊጉን መሪነት በ36 ነጥቦች ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተረክቧል።
በአንጻሩ ኢትዮጵያ ቡና በመሸነፉ ምክንያት ባለበት 32 ነጥብ ላይ የሚቆይ ይሆናል።
የዛሬው ጨዋታ በተለያዩ ድርጅቶች ስፖንሰር በመደረጉና ገቢው ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የሚውል በመሆኑ፥ በርካታ ተመልካቾችን ለማሳተፍ ጨዋታው በሃዋሳ ስታዲየም እንዲደረግ ተወስኗል።
ሊጉን ሲዳማ በ36 ነጥቦች ሲመራ አንድ ጨዋታ የሚቀረው ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ደደቢት እኩል 35 ነጥብ በመያዝ ይከተላሉ።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አዲስ አበባ ከተማ ደግሞ በ15 ግርጌውን ይዘዋል::
የደረጃ ሰንጠረዥ እና ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎችን ይመልከቱ
| # | ክለብ | ተጫ | ልዩ | ነጥብ |
|---|---|---|---|---|
| 1 | ሲዳማ ቡና |
20 | 7 | 36 |
| 2 | ቅዱስ ጊዮርጊስ |
19 | 18 | 35 |
| 3 | ደደቢት |
20 | 11 | 35 |
| 4 | አዳማ ከተማ |
20 | 5 | 34 |
| 5 | ኢትዮጵያ ቡና |
20 | 8 | 32 |
| 6 | ፋሲል ከተማ |
19 | 5 | 29 |
| 7 | አርባምንጭ ከተማ |
20 | 3 | 28 |
| 8 | ሀዋሳ ከተማ |
20 | 0 | 24 |
| 9 | 20 | -1 | 24 | |
| 10 | መከላከያ |
20 | -9 | 24 |
| 11 | ኢትዮ ኤሌክትሪክ |
20 | -1 | 23 |
| 12 | ወላይታ ድቻ |
20 | -7 | 22 |
| 13 | ድሬዳዋ ከተማ |
20 | -8 | 21 |
| 14 | ጅማ አባቡና |
20 | -4 | 20 |
| 15 | አዲስ አበባ ከተማ |
20 | -9 | 15 |
| 16 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ |
20 | -15 | 15 |















አስተያየት ይስጡ