መከላከያ የ2017 የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ቅድመ ማጣሪያ ውድድር የመልስ ጨዋታውን ከሜዳው ውጪ ከካሜሮኑ ዮንግ ስፖርትስ አካዳሚ ጋር ያካሂዳል።
ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ስታዲየም የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታውን ያስተናገደው መከላከያ የካሜሮኑን ዮንግ ስፖርትስ አካዳሚ 1 ለ0 በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል ፡፡
መከላከያ ወደ ዱዋላ ዕረቡ እለት ያመሩ ሲሆን፡፡ ጨዋታውን በሚያደርጉበት ስታዲየም ስታደ ደ ላ ሪዩኒፊኬሽንም ደ ዱዋላ ላይ ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

(Photo-የመከላከያ የፊት መስመር ተጫዋች ሳሙኤል ታዬ ከ ትሬኒንግ መልስ)
መከላከያ ስፖርት ክለብ ዛሬ የመልስ ጨዋታውን ከዮንግ ስፖርትስ አካዳሚ ጋር ከሜዳው ውጭ የሚያደርግ ይሆናል።
ዛሬ 11:30 በካሜሮን ድዋላ በሚያደረገው ጨዋታ በሜዳው ያስመዘገበውን ነጥብ ማስጠበቅ ከቻለ በቀጣይ ከቱኒዚያው ሲ.ኤስ ሴፋክሲያን ስፖርት ክለብ ጋር በመጪው መጋቢት መጀመሪያ የሚጋጠም ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ