መነሻ ገጽ Uncategorized ለካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ፍክክር ኢትዮጵያ አቶ ጁነዲን ባሻህ በመጨረሻው ሠዓት ራሳቸውን ከፉክክሩ ዉጪ(ሪዛይን) አርገዋል
Uncategorized

ለካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ፍክክር ኢትዮጵያ አቶ ጁነዲን ባሻህ በመጨረሻው ሠዓት ራሳቸውን ከፉክክሩ ዉጪ(ሪዛይን) አርገዋል

አጋራ
አጋራ

1a6a5770d85c9e2b1ae6d2c30572f67a

ዛሬ በተካሄደው የካፍ ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የማዳጋስካሩ አህመድ አህመድ የኢሣ ሃያቱን  የ 29 ዓመት አገዛዝ 34 ለ 20 በሆነ ድምፅ በማሸነፍ የኢሣ ሃያቱ ሥርወ መንግሥት መገርሰሱ ይታወሳል።

IMG_20170315_193404

አሁን ከደቂቃዎች በፊት በተጠናቀቀው ለካፍ  ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ፍክክር ኢትዮጵያ አቶ ጁነዲን ባሻህ በመጨረሻው ሠዓት ራሳቸውን ከፉክክሩ ዉጪ(ሪዛይን)በማድረጋቸው ኢትዮጵያ በካፍ የመወከል ዕድሉን ስታጣ ጅቡቲ 1ኛ በመዉጣትዋ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዉስጥ መግባት ችላለች።መጀመሪያ በተደረገው ምርጫ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት በ20 ድምፅ 1ኛ የሱዳኑ ዋና ፀሐፊ በ12 ድምፅ 2ኛ አቶ ጁነዲን ባሻህ በ9ድምፅ 3ኛ የኡጋንዳው በ7ድምፅ መጨረሻ በመውጣታቸውና ከ50 በላይ የሚለውን የምርጫ ህግ ባለማማላቱ ምርጫው እንዲደገም በመወሰኑ 3ኛ የወጡት አቶ ጁነዲን በድጋሚ ቢወዳደሩም መውደቃቸው አይቀሬ መሆኑን በማመን ራሳቸውን ከፉክክሩ በማውጣት ሪዛይን በማድረግ ድምፃቸውን ለጅቡቲው ተወዳዳሪ ሙሉ በሙሉ በመስጠታቸው ማለትም መጀመሪያ ያገኙትን 9 ነጥብ ለጅቡቲ ለመስጠት በመወሰናቸው መጀመሪያ በ20 ድምፅ 1ኛ የነበሩት የጅቡቲው ዕጩ በ29 አጠቃላይ  ድምፅ 1ኛ በመሆን የካፍ ስራ አስፈፃሚ ውስጥ ሲገቡ 12 ድምፅ ያገኙት  የሱዳኑ ዕጩ በ2ተኛነት አጠናቀዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
Uncategorized

ቅዱስ ጊዮርጊስ የመቶ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገለት

ዛሬ አንጋፋውን የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፓርት ማህበር ከገጠመው የመፍረስ አደጋ ለመታደግ የተለያዩ አካላትን...

Uncategorized

ለዋልያዎቹ መጫወትን የሚመኘው የሴሪ ኣው ክለብ ተጫዋች ማነው ?

የጣሊያን ሴሪ ኣው ክለብ ቶሪኖ ንብረት ስለሆነው አስደናቂው የአጥቂ አማካይ ተጫዋች እንንገራችሁ።...

Uncategorized

ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !

  በዛሬው ዕለት ግብ ጠባቂ በማስፈረም ወደ ዝውውሩ የገቡት ኢትዮጵያ ቡናማዎች ዘካሪያስ...