በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ ላይ የተቀመጠው ወልዋሎ አዲግራት በክረምቱ ካስፈረመው ተከላካይ ጋር በጋራ ስምምነት መለያየቱ ተሰማ።
ወጣቱ የመሐል ተከላካይ ታዬ ጋሻው በክረምቱ ወደ ወልዋሎ በማምራት ላለፉት ወራቶች በክለቡ ጥሩ ጊዜን አሳልፏል።
ከክለቡ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች መሃል አንዱ የሆነው ታዬ ትላንት ከክለቡ ጋር በተደረገ ስምምነት ቀሪ የውል ዘመን እየቀረው በጋራ ስምምነት ውላቸውን በይፋ ቀደዋል።
የአዳማ ከተማ ወጣት ቡድን ፍሬ የሆነውና ወደ ዋናው ቡድን ያደገው ተጨዋቹ ወደ ነገሌ አርሲም ተዛውሮ ተጫውቷል።
ተጨዋቹ ከነገሌ አርሲ በድጋሚ ወደ አሳዳጊ ቡድኑ ተመልሶ ለ2 ዓመታት ለክለቡ በወጥ አቋም ግልጋሎትን ሰጥቷል።
- ማሰታውቂያ -
ተጫዋቹም በቅርቡ ወደ ሌላ የሊጉ ክለብ ሊያመራ እንደሚችል ሀትሪክ ስፖርት ያገኘው መረጃ አመላክቷል።


