አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ እና ጅቡቲ ብሔራዊ ቡድኖች ለሚጠብቀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል።
በስብሰቡም ለረጅም ጊዜ በጉዳት ምክንያት ከሜዳ የራቀው የሱፐር ስፖርት ዩናይትዱ አቡበከር ናስርም ጥሪ ተደርጎለታል።
በተጨማሪም ለበርካታ ወረቶች ከሜዳ ርቆ የነበረው የፋሲል ከነማው ሀብታሙ ተከስተም በዋልያው ስብስብ ውሰጥ ተካቷል።
በግብ ጠባቂነት: አቡበከር ኑራ ፣ ሰይድ ሀብታሙ እና ቢንያም ገነቱ ተመርጠዋል።
- ማሰታውቂያ -
በተከላካይ ስፋራ : ብርሀኑ በቀለ ፣ አስራት ቱንጆ ፣ አህመድ ረሺድ ፣ ያሬድ ካሳዬ ፣ አብዱሰላም የሱፍ ፣ ራምኬል ጀምስ ፣ አማኑኤል ተርፋ ፣ ፍሬዘር ካሳ ፣ ወልደአማኑኤል ጌቱ እና አስቻለው ታመነ ተካተውበታል።
በአማካይ ስፋራ : አማኑኤል ዮሐንስ ፣ በረከት ወልዴ ፣ አብዱልከሪም ወርቁ ፣ ወገኔ ገዛኸኝ ብሩክ ማርቆስ እና ሀብታሙ ተከስተ ተመርጠዋል።
በአጥቂ ስፋራ : አቡበከር ናስር ፣ ቸርነት ጉግሳ ፣ በረከት ደስታ ፣ አህመድ ሁሴን እና መሐመድ አበራ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ናቸው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር መጋቢት 12 እንዲሁም ከጅቡቲ አቻው ጋር መጋቢት 15 በሞሮኮ ጨዋታዎቹን ያደርጋል።


