በሊጉ አንድም ጨዋታ ማሸነፍ ያልቻለው ወልዋሎ ለዋና አሰልጣኙ እና ለቡድኑ አባላት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያን ሲሰጥ አንዱን ግን አሰናብቷል።
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ካለፈው አመት መማር ሳይችሉ ከቆሙበት ዘንድሮም የቀጠሉት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሀያ ቡድኖች መካከል እየተደረገ በሚገኘው ፕሪምየር ሊግ ካደረጓቸው ሰባት ጨዋታዎች በስድስቱ ተሸንፈው በአንድ ብቻ ነጥብ ተጋርተው በአንድ ነጥብ የደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ ላይ መቀመጥ ችለዋል።
ግርማ ታደሠ (መንቾን) በዋና አሰልጣኝነት ቀጥሮ እየተመራ የሰነበተው ክለቡ በውጤት እጦት ምክንያት እየተጓዘ መሆኑን ተከትሎ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት በቀጣይ ጨዋታ ማሸነፍ ካልቻሉ ከሀላፊነት እንዲሰናበቱ የክለቡ ቦርድ መወሰን የቻለ ሲሆን ረዳት አሰልጣኙ እና ባለፈው አመት የመጨረሻዎቹን አመታት ዋና አሰልጣኝ የነበሩት አታክልቲ በርሄ ሲሰናበቱ ሌሎቹ ረዳቶች የቀድሞው የአርባምንጭ አሰልጣኝ ጳውሎስ ፀጋዬ ፣ የግብ ጠባቂ አሰልጣኙ ቢኒያም ተረፈ ፣ የአካል ብቃት አሰልጣኙ አብረሀ ታሀረ እና ቡድን መሪው ሀዲ አህመድ በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ታልፈዋል።
ትላንት በወላይታ ድቻ ሽንፈት ያስተናገደው ቡድኑ በቀጣይ በትግራይ ደርቢ መቐለን ማሸነፍ ካልቻለ የአሰልጣኙ እህል ውሀ የሚቋጭ ይሆናል።


