መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ የጨዋታ ማጭበርበር ተካሂዶብኛል ሲል ከሰሰ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግወልቂጤ ከተማዜናዎች

ወልቂጤ ከተማ የጨዋታ ማጭበርበር ተካሂዶብኛል ሲል ከሰሰ

አጋራ
አጋራ

በኢትዮዽያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ሻምፒዮኑ ፋሲል ከነማን 3 ለ1 መርታቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ ላይ ቅሬታዎች እየተሰሙ ነው።

በተለይ በድሬዳዋ ማሽነፍ ቀጥተኛ ተጎጂ የሆነው ወልቂጤ ከተማ “ፋሲል ከነማ ሆን ብሎ ድሬዳዋ ከተማን ለመጥቀም ከአቅም በታች በመጫወት የጨዋታ ማጭበርበር በመፈጸሙ የተቀረጸውን ቪዲዮ በማየት በገለልተኛ ወገን እንዲጣራና ርምጃ እንዲወሰድ እንጠይቃለን” ሲል የኢትዮዽያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን አሳስቧል።

“ቅራኔ የሚፈጥረውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት የሀገራችንን ክለቦች ሰላማዊ ግንኙነት የሚያበላሽና ጥቁር ነጥብ የሚያስጥለውን የፋሲል ከነማ ድርጊት እንዲመረመር እንጠይቃለን” ያለው ወልቂጤ ከተማ “የብሄራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት በመራ አሰልጣኝ መከወኑ ከወር በፊት ኒጀር ስፖርታዊ ጨዋነትን ተከትላ ማሽነፏ ብሄራዊ ቡድናችን ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን በመርሳት ስነምግባር በሌላቸው የብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋቾች መፈጸሙ በስነምግባራቸው ምስጉን የሆኑ አሰልጣኞችና ተጨዋቾችን አንገት ያስደፋ ድርጊት ነው” በማለት ኮንኖ ህጋዊ መፍትሄ እንዲሰጠው ጠይቋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...