መነሻ ገጽ ሊግ ካምፓኒ የ ዲ ኤስ ቲቪ የቡድን አባላት ተሸነፉ
ሊግ ካምፓኒቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችዲ ኤስ ቲቪ

የ ዲ ኤስ ቲቪ የቡድን አባላት ተሸነፉ

አጋራ
አጋራ

የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በተለያዩ ከተሞች መካሄዱን አስመልክቶ የ ዲ ኤስ ቲቪ የቡድን አባላት በተለያዩ ጊዜያት ጨዋታቸውን እንደሚያካሂዱ ይታወቃል ።

ይህንንም ተከትሎ በዛሬው ዕለት የ ዲ ኤስ ቲቪ  ሙሉ የቡድን አባላት ከ ከዋልያዎቹ የአሰልጣኞች ክፍል እና ከ ሊግ ካምፓኒው ሙሉ የቡድን አባላት ጋር ጨዋታቸውን በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ማካሄድ ችለዋል ።

አዝናኝ በነበረው እና አስራ ስድስት ጎሎች በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የ ዲ ኤስቲቪ አባላት 9 ለ 7 በሆነ ውጤት ሽንፈትን ቀምሰዋል ።

የዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ አራት ጎሎችን ከመረብ በማሳረፍ ቁልፍ ሚናን ሲጫወቱ የ ዲኤስቲቪ የካሜራ ባለሙያው ብሩክ መክብብ በተቃራኒው ሀትሪክ መስራት የቻለ ተጫዋች ሆኗል ።

የ ዲኤስቲቪ የጨዋታ አስተላላፊ የሆኑት ጋዜጠኛ ሰዒድ ኪያር ሁለት ጎሎችን እንዲሁም ጋዜጠኛ መኮንን ሀይሉ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ በማቀበል ሀትሪክ መስራት ችሏል ።

በዚህ ጨዋታ ላይ የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሀም መብርሀቱን ጨምሮ የ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ ሀያ አመት በታች ዋና አሰልጣኝ ተመስገን ዳና በስታዲየም በመገኘት ጨዋታውን መታደም ችለዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...