መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ የዋልያዎቹ ጋዜጣዊ መግለጫ !
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የዋልያዎቹ ጋዜጣዊ መግለጫ !

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወቅታዊ ሁኔታ እንዲሁም የነገውን ጨዋታ አስመልክቶ ከደቂቃዎች በፊት በፌዴሬሽኑ ፅ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል ፡፡

የፌዴሬሽኑ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን እንዳሳወቁት የነገውን ጨዋታ ከሰባ ያልበለጡ ታዳሚያን ብቻ እንደሚመለከቱት ገልፀዋል ፡፡ ይህንንም ተከትሎም ከሚዲያ ተቋማት የተመረጡ ሀያ ባለሙያዎች ብቻ እንዲሁም ሀምሳ የ ቪ አይ ፒ ሰዎች ጨዋታውን እንደሚታደሙ ተገልፆል ፡፡

በመግለጫው ተያይዞ ሲገለፅም ካፍ በአዲስ አበባ ስታዲየም ጨዋታው እንዲደረግ ሲፈቅድ 20 % የስታዲየም ተመልካች እንዲገባ በፌዴሬሽኑ የቀረበው ጥያቄ ውድቅ መደረጉን ገልፀዋል ፡፡

ከአዲስ አበባ ስታዲየም እድሳት ጋር ተያይዞ አቶ ባህሩ ጥላሁን በሰጡት አስተያየት “የአዲስ አበባ ስታዲየምን ለማደስ ብናስብ እንኳ አቅሙም የለንም የዕድሳት ሃላፊነቱ የስፖርት ኮሚሽኑ ነው፡፡ የስታዲየሙ ባለቤት ስፖርት ኮሚሽን ሲሆን ሜዳውን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ትራኩን አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያስተዳድሩታል ” ሲሉ በጉዳዩ ላይ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል ፡፡

በነገው ዕለት የሚካሄደው ጨዋታ የቀጥታ ስርጭት ሽፋንን እንደማያገኝ በመግለጫው ላይ ይፋ ተድርጓል ፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...