መነሻ ገጽ ዋልያዎቹ የአምስቱ የኮቪድ 19 ተጠቂ ተጨዋቾች ውጤት ዛሬ ይታወቃል…
ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

የአምስቱ የኮቪድ 19 ተጠቂ ተጨዋቾች ውጤት ዛሬ ይታወቃል…

አጋራ
አጋራ

የአምስቱ የኮቪድ 19 ተጠቂ
ተጨዋቾች ውጤት ዛሬ ይታወቃል…

*… ዋሊያዎቹ ተደናግጠዋል…..

የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሰጠው ማሳሰቢያ
ከነበሩበት ሆሊዴይ ሆቴል ወጥተው ዋሊያዎቹ ወዳሉበት ካፍ አካዳሚ የተመለሱት 5ቱ የኮቪድ 19 ተጠቂ ተጨዋቾች ትላንት በድጋሚ መመርመራቸው ታውቋል፡፡

ተጨዋቾቹ ሙሉ በሙሉ ነጻ መሆናቸው ሳይታወቅ ወደ አካዳሚው እንዲመጡ ሲደረግ ነጻ የሆኑት ተጨዋቾች መደንገጣቸው ታውቋል፡፡ ፌዴሬሽኑ ተጨዋቾቹን ለማስመርመር ገስት ሀውስ የፈለገ ቢሆንም አካዳሚው የተሻለ አማራጭ በመሆኑ ሌሎቹ ተጨዋቾችን ሳይጠጉ ራቅ ባለ ክፍል ውስጥ እንዲያርፉ አድርጓል፡፡ ያም ቢሆን ታዲያ ነጻ የሆኑት ቀሪዎቹ ተጨዋቾች ፍርሃት እንደተሰማቸው መረጃውን ከተጨዋቾቹ አግኝቻለሁ፡፡
በአሁኑ ወቅት አምስቱ ተጨዋቾች በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን የድጋሚ ምርመራ ውጤታቸው ነጻ መሆናቸውን ካሳየ ደግሞ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በሚኖረው የልምምድ ሰአት ላይ ቡድኑን ተቀላቅለው በግላቸው ልምምድ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...