መነሻ ገጽ ከ 20 ዓመት በታች ሴቶች “ሴቶችንና አገሪቷን አክብራችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ” አሰልጣኝ ፍሬው ሃ/ገብርኤል የ20 አመት ሴቶች ብ/ቡድን አሰልጣኝ
ከ 20 ዓመት በታች ሴቶችዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

“ሴቶችንና አገሪቷን አክብራችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ” አሰልጣኝ ፍሬው ሃ/ገብርኤል የ20 አመት ሴቶች ብ/ቡድን አሰልጣኝ

አጋራ
አጋራ

” ተጨዋቾች የአሰልጣኝ ብርሃኑም ሆነ የኔ አይደሉም የኢትዮጵያ ናቸው ተናበን መስራት የግድ ነው”

“ሴቶችንና አገሪቷን አክብራችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ”

አሰልጣኝ ፍሬው ሃ/ገብርኤል
የ20 አመት ሴቶች ብ/ቡድን አሰልጣኝ

20 አመት ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለኮስታሪካ የአለም ዋንጫ ለማለፍ ከሩዋንዳ ጋር ላለው ጨዋታ ነገ ጠዋት ወደ ኪጋሊ ያቀናሉ።

የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ፍሬው ሃይለ ገብርኤል በፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት በሰጡት መግለጫ ለ22 ቀናት ልምምድ ማድረጋቸውና ወደ 40 ተጨዋቾች ይዘው ሲሰሩ እንደነበር ገልጸዋል።”

ከውድድር ላይ በመጡ ጊዜ ለቡሩንዲ ጨዋታ የሰራነው ልምምድ ከ15 ቀን የማይበልጥ በመሆኑ የአሁኑ ይሻላል የአሁኑ ጊዜው 22 ቀን ቢሆንም ከውድድር ስላልመጡ ትግል ነበረው” ሲሉ ተናግረዋል። አሰልጣኙ “40 ተጨዋቾች መርጠው ልምምድ ከሰሩ በኋላ ሁለት ተጨዋቾች በግል 3 ተጨዋቾቾ በጉዳት፣ 7 ተጨዋቾች በአቋም መውረድ የተቀነሱ ሲሆን ወደ ሩዋንዳ ከመጓዛችን በፊት ሌሎች 7 ተጨዋቾችን እንቀንሳለን” ሲሉ አስረድተዋል።

አሰልጣኙ የሩዋንዳ ቡድንን በተመለከተ “ባለፉት ሁለት አመታት ምንም አይነት ጨዋታ ስላልነበር ስለ ሩዋንዳ ምንም መረጃ የለኝም ስለዚህ የአሰልጣኝ ልዩነት ብዬ በማስበው የግጥሚያው ቀን ግጥሚያውን አይቼና አንብቤ ለማሸነፍ የማደርገው ጥረት ነው”ሲሉ አስረድተዋል።

ከሉሲዎቹ አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው ጋር ትናበባላችሁ ወይ የተባሉት አሰልጣኝ ፍሬው” ባለፉት አመታት ውድድር ስላልነበር መናበብ አልቻልንም ለቀጣዩ ግን በግሌ ዝግጁ ነኝ ተጨዋቾች

የአሰልጣኝ ብርሃኑ ወይም የኔ አይደሉም የኢትዮጵያ ናቸው ተናበን መስራት የግድ ነው”ሲሉ መልሰዋል። መግለጫው ላይ ለተገኙት ቁጥራቸው ላነሰ ጋዜጠኞች “ሴቶችንና አገሪቷን አክብራችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ” ያሉት አሰልጣኙ ” ስለዝግጅቴ መሟላት አለመሟላት ምንም ማለት አልሻም በተቻለ መጠን የችግር ሳይሆን የመፍትሄ አካል መሆን ነው የምፈልገው”ሲሉ ተናግረዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...