መነሻ ገጽ ከ 20 ዓመት በታች ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት ብሔራዊ ቡድን ጨዋታቸውን አካሄዱ !
ከ 20 ዓመት በታችዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት ብሔራዊ ቡድን ጨዋታቸውን አካሄዱ !

አጋራ
አጋራ

በዛሬው ዕለት ረፋዱን ከቀናት በፊት በተያዘ ቀነ ቀጠሮ የሁለቱ መርሐ ግብር ሲካሄድ ጨዋታው ያለ ምንም ግብ አቻ ለመውጣት ችለዋል ፡፡
የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በ አሰልጣኝ ተመስገን ዳና በዛሬው ጨዋታ ሁለት ቡድኖች ይዘው ሲቀርቡ ከፊታችን ለሚጠብቃቸው የሴካፋ አልፎም ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚካሄደው የውድድር መድረክ ላይ ቡድናቸውን አይተውበታል ተብሎ ይጠበቃል ፡፡

ብሔራዊ ቡድኑ ለ ሰላሳ ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበው ልምምዳቸውን አጠናክረው ሲቀጥሉ በነገው ዕለትም በአዲስ አበባ ስታዲየም ተመሳሳይ የልምምድ መርሐ ግብራቸውን የሚቀጥሉ ይሆናል ፡፡
የፈረሰኞቹ አሰልጣኝ ቡድኑን ከተረከቡ በኋላ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ማካሄድ ሲችሉ በዝውውር መስኮቱ ቡድኑን መቀላቀል የቻለው አዲስ ግደይ የመጀመሪያ ጨዋታውን ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል ፡፡

ኤርነስት ሚደንድሮፕ በዛሬው ጨዋታ ላይ ፓትሪክ ማታሲ ፤ አብድልከሪም መሐመድ ፤ ሄኖክ አዱኛ ፤ ምንተስኖት አዳነ ፤ ፍሪምፖንግ ሜንሱ ፤ ሙሉዓለም መስፍን ፤ ደስታ ደሙ ፤ ያብስራ ተስፋዬ ፤ አዲስ ግደይ ፤ ፀጋዬ ፤ አቤል ያለው በመጀመሪያ አሳላለፍ ውስጥ መካተታቸውን ለማወቅ ተችሏል ፡፡

ተመስገን ዳና ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ከ ሀትሪክ ስፖርት ጋር ቆይታን ሲያደርግ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብን ሲያመሰግኑ በሀለቱም አጋማሾች የተለያዩ ተጫዋቾችን መሞከራቸውን ገልፀውልናል ፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...