በኮስታሪካ አዘጋጆነት ለሚደረገዉ የ2022 ከ20 አመት በታች የሴቶች አለም ዋንጫ ለመሳተፍ የማጣሪያ ዉድድራቸዉን እያደረጉ የሚገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአራተኛው ዙር የታንዛኒያን ብሔራዊ ቡድን እንደሚገጥሙ ታዉቋል።
በሶስተኛው ዙር የማጣሪያ ጨዋታ የቦትስዋና አቻቸዉን በደርሶ መልስ ዉጤት 8ለ2 በመርታት ወደ ቀጣዩ ዙር የተሻገሩት የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን በተመሳሳይ በድምር ዉጤት ቡርንዲን አሸንፋ ወደ ቀጣዩ ዙር የተሻገረችውን ታንዛኒያን እንደሚገጥሙ ተረጋግጧል።
አስተያየት ይስጡ