መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | ዳዋ ሆቴሳ አዳማ ከተማን ከሽንፈት ታድጓል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአርባምንጭ ከተማአዳማ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ዳዋ ሆቴሳ አዳማ ከተማን ከሽንፈት ታድጓል

አጋራ
አጋራ

በስምንተኛው ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ በቀዳሚነት የተገናኙት አርባምንጭ ከተማ እና አዳማ ከተማ ሲሆኑ ለ80 ያህል ደቂቃዎች 1 ለ 0 ሲመሩ የቆዩት አዞዎቹ በተጨማሪ ሰዓት በተቆጠረባቸው ግብ አቻ ተለያይተው ለመውጣት ተገደዋል ።

አርባምንጭ ከተማ በሰባተኛው ሳምንት ከጅማ አባጅፋር አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ከነበረው ቋሚ አስራአንድ የአራት ተጫዋቾች ቅያሪ በማድረግ ወርቅይታደስ አበበ ፤ አንድነት አዳነ ፤ መላኩ ኤልያስን እና ኤሪክ ካፓይቶን ወደ አሰላለፍ ሲመልሱ በአዳማ ከተማ በኩል ደግሞ አዳማ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ከተጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ ሁለት ቅያሪ በማድረግ ኤልያስ ማሞን እና ጅብሪል አህመድን በቋሚ አሰላለፉ ማካተት ችለዋል ።

ለአይን ሳቢ በሆነ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተጀመረው ጨዋታ በተለይም በአዞዎቹ የማጥቃት አጨዋወት የታጀበ ነበር ። በከባድ የማጥቃች አጨዋወት የቀጠሉት አርባ ምንጭ ከተማዎች ግብ ለማስቆጠር 10 ደቂቃዎች ብቻ ነበር የፈጀባቸው ። በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ ሙና በቀለ ከመስመር ያሻገረውን ኳስ ኬንያዊው ኤሪክ ካፓይቶ በግንባር ገጭቶ በማስቆጠር አዞዎቹን ቀዳሚ ማድረግ ቻለ ። መሪዎቹ አርባምንጭ ከተማዎች በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ፊት የሚያደርጉት ጥረት ለአዳማ ከተማ ተከላካዮች ከባድ ፈተና ሆኖባቸው ነበር ።

አዳማ ከተማዎች በጥቂት አጋጣሚዎች ወደ ፊት ሄደው ጫና ለመፍጠር ያደረጉት ጥረት በአርባምንጭ ተከላካዮች የከሸፈ ሲሆን 36ኛ ደቂቃ ላይ ግን በአሜ መሀመድ አማካኝነት ከቅጣት ምት በተነሳ ኳስ ያደረጉት የግብ ሙከራ በግብ ጠባቂው ተመልሷል ። በመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ አዳማ ከተማዎች ወደ ግብ በመድረስ የተሻሉ መሆን ችለው ነበር ። በዚህም 38ኛ ደቂቃ ላይ አበዲሳ ጀማል በሳጥን ውስጥ ሆኖ ከአሜ መሀመድ የደረሰውን ከግብ ጠባቂው የተተፋ ኳስ ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ በአጨራረስ ድክመት ሳያስቆጥረው ቀርቷል ። የመጀመሪያው አጋማሽም በአርባምንጭ ከተማ መሪነት ተጠናቀቀ ።

የሁለተኛው አጋማሽ አዳማ ከተማዎች በተወሸነ መልኩ የበላይ ሆነው የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር የሞከሩበት ነበር ። 53ኛ ደቂቃ ላይ ሀቢብ ከማል ከቅጣት ምት ወደ ግብ የሞከረውን ኳስ ግብ ጠባቂው ጀማል ጣሰው መልሶ የማዕዘን ምት አድርጎታል ። ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ተቀይሮ የገባው አቡበከር ወንድሙ ከመስመር የተሻገረለተን ኳስ ለማስቆጠር ያደረገው ጥረት በግብ ጠባቂው ይስሀቅ ተመልሶበታል ።

አርባምንጭ ከተማዎች በአመዛኙ በራሳቸው ሜዳ ላይ ሆነው በመጫወት ያገኟትን ግብ አስጠብቀው ለመውጣት ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን 77ኛ ደቂቃ ላይ ተበይሮ የገባው አቡበከር ሻሚል ግብ ጠባቂውን አልፎ ያመከነው ኳስ ለአዞዎቹ አስቆጪ ነበር ። የአቻነቷን ግብ ለማግኘት ከፍተኛ ጫና በማድረግ ላይ የነበሩት የፋሲል ተካልኝ ልጆች ድካማቸው ባለቀ ሰዓት ፍሬ አፍርቶላቸዋል ። ከቅጣት ምት የተመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው ይስሀቅ ተገኝ መቆጣጠር ሳይችል ቀርቶ ኳሱ የደረሰው ዳዋ ሆቴሳ አስቆጥሮ አዳማ ከተማዎችን ከሽንፈት ታድጓል ።

ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ ነጥቡን 11 በማድረስ በግብ ክፍያ ተበልጦ 8ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ አዳማ ከተማ ደግሞ በ9 ነጥብ ወደ 11ኛ ደረጃ ከፍ ብሏል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...