በ2018 ዓ.ም ነሀሴ ወር ላይ በፖላንድ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ ድልድል ይፋ ሆኗል።
በድልድሉ የኢትዮጵያ ሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሁለተኛው ዙር የማጣሪያ ጨዋታ ከኬንያ አቻው ጋር ተደልድሏል።
የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የደርሶ መልስ ጨዋታዎች በቀጣዩ ዓመት መስከረም ወር ላይ ይደረጋሉ።
የኢትዮጵያ የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የኬንያ አቻውን በደርሶ መልስ ማሸነፍ ከቻለ በሶስተኛው ዙር ማጣሪያ ከታንዛኒያ እና አንጎላ አሸናፊ ጋር ይጫወታል።
- ማሰታውቂያ -
በ2024 የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጨረሻው ዙር ማጣሪያ በሞሮኮ አቻው ተሸንፎ ወደ ውድድሩ ማለፍ ሳይችል መቅረቱ ይታወሳል።



