እ.አ.አ በ2026 በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚደረገው 16ኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ድልድል ከደቂቃዎች በፊት ይፋ ሆኗል።
በድልድሉ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው ዙር የማጣሪያ ጨዋታ ከኡጋንዳ አቻው ጋር ተደልድሏል።
የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ከየካቲት 10 እስከ የካቲት 20 ድረስ ባሉ ቀናት መካከል ይደረጋሉ።
ሉሲዎቹ የኡጋንዳ አቻቸውን በደርሶ መልስ ማሸነፍ ከቻሉ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ከታንዛኒያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አሸናፊ ጋር ይጫወታሉ።
- ማሰታውቂያ -
በማጣሪያው 38 ሀገራት ተሳታፊ ሲሆኑ 12 ሀገራት በዋናው ውድድር ላይ ተሳታፊ ይሆናሉ።
ከ15 የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች በሶስቱ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ በተደረገው የ2004 ውድድር በአራተኝነት ያጠናቀቀበት ትልቁ ውጤቱ ነው።
ሉሲዎቹ እ.አ.አ በ2012 በኢኳቶሪያል ጊኒ በተዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ከተሳተፉ በኋላ በአህጉራዊው ውድድር ላይ መገኘት አልቻሉም።



