በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
መቀለ 70 እንደርታ አራተኛው ወራጅ ክለብ ሆኗል።
ወልዋሎ አዲግራት ስሁል ሽረና አዳማ ከተማ ቀድመው የወረዱ ሲሆን መቀለ 70 እንደርታ በኢትዮ ኤሌክትሪክ 1ለ0 ተሸንፎ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።
ከአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ሃላፊነት ተረክቦ ወልዋሎን ቢይዝም ወራጅ ከመሆን ያላተረፈው አሰልጠኝ ጸጋዬ መቀለ 70 እንደርታን ከአሰልጣኝ ዳንኤል ጸሃዬ እጅ ተረክቦ በአንድ አመት ውስጥ ሁለቱንም ክለቦች ያወረደ አሰልጣኝም ሆኗል።
ሶስቱ የትግራይ ክለቦች በአስተዳደራዊ ውሳኔ ወደ ውድድሩ ቢመለሱም በደንብ ተዘጋጅቸውና ጠንካራ ተፎካካሪ የሚያደርጓቸውን ተጨዋቾች ሳያስፈርሙና ሳይዘጋጁ መምጣታቸው ጎድቷቸዋል። የሊጉን ዋንጫ ካነሱ 10 ክለቦች መሃል አንዱ የሆነው መቀለ 70 እንደርታ ወደታችኛው ሊግ መውረዱ ደጋፊዎቹን አሳዝኗል።
- ማሰታውቂያ -
ከፍተኛ በጀት በሚያስፈልግበት ጊዜ በጋዜጠኛ ኤፍሬም የማነ ኢ.ዋይ ፕሮዳክሽን ተቋም በተዘጋጀውና ስፖርት ለሰላም ስፖርት ለሀገር አንድነት በሚል መርህ ከጦርነት ማግስት ከመፍረስ ለማዳን ክለቦቻችንን እንታደግ በሚል መሪ ቃል ለትግራይ ክለቦች የገቢ መሰባሰቢያ መርሃግብር በሸራተንና በስካይ ላይት ሆቴሎች ካካሄደ አንድ ዓመት ቢሞላውም ቃል የተገባው ገንዘብ በሚገባ አለመሰብሰቡና ቃላቸው አለመተግበሩ ቡድኖቹ በአግባቡ በፋይናንስም ባለመጠናከራቸው እንደማሳያ ተደርጎ ተወስዷል። በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ዙሪያ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ሂደቱን በተመለከተ ለሀገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን በሙሉ በይፋ በቅርቡ መግለጫ እንደሚሰጡም ለሀትሪክ አሳውቀዋል።
በዘንድሮ ውጤት መሰረት በ2018 እግርኳስ ወዳዱ የትግራይ ስፖርት ቤተሰብ የክልሉ ክለቦች የሌሉበት ፕሪሚየር ሊግ ለማየት መገደዳቸው አሳዛኝ ሆኗል።


