▻ በዛሬው እለት በ ቅዱስ ጊዮጊስ ተስፋ ቡድን ድንቅ እንቅስቃሴ በማድረግ ወደ ዋናው ቡድን በማደግ መጫወት የቻለው ሀብታሙ ጉልላት እንግዳችን አድርገን አቅርበናል ።
ሀትሪክ : በቅድሚያ ሀትሪክ ስፖርት ቃለመጠይቅ ለማድረግ ፍቃደኛ ስለሆነ እናመሰግናለን
ሀብታሙ : እኔም አክብራቹ ስለጋበዛቹኝ አመሰግናለው
ሀትሪክ : እግር ኳስ እንዴት ጀመርክ ??
- ማሰታውቂያ -
ሀብታሙ : እግር ኳስን እንደማንኛውም ታዳጊ ሰፈር ውስጥ በመጫወት ነው የጀመርኩት
ሀትሪክ : ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዴት ተቀላቀልክ ?
ሀብታሙ : ቅዱስ ጊዮርጊስን 2015 ዓ.ም በወጣው ምልመላ ነበር የተቀላቀልኩት ።
ሀትሪክ : በቅዱስ ጊዮርጊስ ተስፋ ቡድን የነበረህን ቆይታ እና ድሎች እስኪ ግረፃቸው
ሀብታሙ; በጣም ደስ የሚሉ እንዲሁም ትልቅ መሻሻሎችን ያገኘሁበትን 2 ዓመታቶች በቅዱስ ጊዮርጊስ ተስፋ ቡድን አሳልፌአለው ታዳጊ ሆኖ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ማለፍ ለየትኛውም ታዳጊ ህልም ነው እና ጥሩ ቆይታ ነበረኝ እንዲሁም በመጀመሪያ ዓመቴ ላይ የተሰጡኝን እድሎች እራሴን እንዳሻሽል እረድተውኝ በቀጣዮ አመት የነበሩትን ሁሉንም ጨዋታዎች መጫወት ችያለው ብዙ ጎሎችንም ማስቆጠር ችያለው ።
ሀትሪክ : ወደ ዋናው ቡድን በ ሰንት ዓመተ ምህረት አደክ ??
ሀብታሙ : ተስፋው ቡድን ላይ 2015 እና 2016ን ከተጫወትኩኝ በሁዋላ በ2017 ዋናውን ቲም መቀላቀል ችያለው ።
ሀትሪክ : የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችን እንዴት ትገልፃችዋለህ ?
ሀብታሙ : መሸነፍን የሚጠሉ ቲማቸው እንዲያሸንፍ የትኛውነም ዋጋ መክፈል የሚችሉ ከደጋፊም በላይ ቤተሰብ የሚለው ይገልፃቸዋል ።
ሀትሪክ : በእግር ኳስ ሮል ሞዴሌ ብለህ ማንን ትጠቅሳለህ
ሀብታሙ : በብዙ መውደቅና መነሳት አልፎ እዚ የአለም ምርጥ መሆን የቻለውን ክርስቲያኖ ሮናልዶን አድናቂውም እሱንም እያየው ያደኩት ።
ሀትሪክ : የታላቁን ክለብ ማለያ በመልበስ ምን አይነት ስሜት ተሰማ ?
ሀብታሙ : ይሄ ማልያ የድል ማልያ ነው ይሄንን ማልያ መልበስ የአሸናፊነት ስሜት መላበስ ነው እና ይሄንን ማልያ መልበስ ትልቅ ኩራት ነው ።
ሀትሪክ : የዘንድሮ የውድድር ዓመት እንዴት አየህው ??
ሀብታሙ : የዘንድሮ የውድድር ዓመት ህብረትና አንድነታችንን የሚጠይቅ ነበር እና ያ ስሜት እነዲኖረን ከአሰልጣኞቻችን ጀምሮ ልምድ እስካላቸው ተጫዋቾች ያደረጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነበር እናም ልፋታቸው ተሳክቶ ሜዳ ውስጥ መሸነፍ የማይፈልግ ለክብሩ እና ለማልያው የሚጫወት ወጣት ቲም ገንብተን የልፋታችንን ያህል አግኝተናል ባንልም ከሞላ ጎደል ጥሩ ዓመት ነበረን ብዬ አስባለው
ሀትሪክ :በቀጣይ ከ ቡድንህ ጋር ምን ታስባለህ ?
ሀብታሙ : በቀጣይ ከጓደኞቼ እና ከአሰልጣኞቻችን ጋ በመሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ የለመደውንና ባህሉ የሆነውን አሸነናፊ ቡድን ገንብተን ወደ ቀድሞ ክብሩ መመለስ እና ዋንጫዎችን ማሳካት እፈልጋለው ።
ሀትሪክ : ወደ ጨዋታዎች እንምጣ : ሀብታሙ የማን አድናቂ ነው ከ ሀገር ውስጥ ከ ሀገር ውጭ በተጨማሪም ከ ሀገር ውጭ ቡድን ማንን ትደፋለህ ?
ሀብታሙ : ከሀገር ውስጥ ሽመልስ በቀለ
ከውጪ ቲያጎ አልካንትራ አድናቂ ነኝ ከ ቡድን የ አርሰናል ደግፋለሁ ።
ሀትሪክ ; በትርፍ ሰዓት ምን ያዝናናሀል ?
ሀብታሙ : ከጓደኞቼ እና ከቤተሰቦቼ ጋር ማሳለፍ ያዝናናኛል ።
ሀትሪክ : እግር ኳስ ተጫዋቾች ባትሆን ምን ትሆን ነበር ?
ሀብታሙ : ምናልባት ጠበቃ ልሆን እችል ነበር
ሀትሪክ : ማመስገን መትፈልጋቸው አካላት ካሉ እድሉን እንስጥህ በመጨረሻ
ሀብታሙ : በቅድሚያ ቤተሰቦቼን ማመስገን እፈልጋለው በመቀጠል አሰልጣኝ አበበ ተስፋዬ :ብሩክ ታረቀኝ:ቢንያም(ታጠቅ):አሰልጣኝ ሳምሶን(ሳሚ ፍሌክስ)አዳነ ግርማ: አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ከልጅነት እስካሁን እስካለሁበት ከጎኔ የነበሩ ሰዎች ናቸውና ከልቤ ላመሰግናቸው እፈልጋለው።
ሀትሪክ : ፍቃደኛ ሆነህ ቃለመጠይቅ ስላደረክ በድጋሚ ከልብ እናመሰግናለን መልካም የእረፍት ጊዜ !
ሀብታሙ : እኔም አመሰግናለው


