የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ካደረገው አስቸኳይ የቦርድ ስብሰባ በኋላ ባለ አምስት ነጥብ መግለጫ አውጥቷል።
በኢትዮጵያ ዋንጫ ቡድኑን ለመደገፍ ከወላይታ ወደ አዲስ አበባ በለሊት የተጓዙ ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም ባለመግባታቸው ቦርዱ ይቅርታ ጠይቋል።
በተጨማሪም ቡድኑ ከሲዳማ ቡና ጋር በገለልተኛ ሜዳ በአዲስ አበባ ለመጫወት ለፌዴሬሽኑ ጥያቄ አቅርቦ ጥያቄው ተቀባይነት አግኝቶ ውድድሩ ሊደረግ ቀን ተቆርጦለት እና ባልተጠበቀ ሁኔታ በዕለቱ ጨዋታው በዝግ እንዲካሄድ በመጨረሻ ሰዓት በተላለፈ ውሳኔ መሰረት በክለቡ ደጋፊዎች ላይ የደረሰውን እንግልት እና ሞራል ለፌዴሬሽኑ እና ለሊግ ካምፓኒው ማቅረቡን ቦርዱ የገለፀ ሲሆን ደንቦቹ እንዲታዩ እና ሕጋዊ ወሳኔ እንዲሰጥ መጠይቁን አስታውቋል።
- ማሰታውቂያ -
ቡድኑ በጨዋታው የገሀድ ስህተቶች ተፈፀሙብኛል ያለ ሲሆን ከነዚህም መሀከል :- በሊግ ካምፓኒው ተቀተው ቅጣት ላይ የነበሩ ተጨዋቾች ተሰለፈው ተጫውተዋል ፤ የገባ ጎል ከጨዋታ ውጭ ነው ተብሎ ተሽሮብናል ፤ የፍፁም ቅጣት ምት ተከልክለናል እንዲሁም በተደጋጋሚ በዳኞች በደል ደርሶብናል በማለት የገለፀ ሲሆን ቦርዱም የቀረበውን መረጃ እና ማስረጃ በመከታተል ወሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል።
እንዲሁም ኢትዮጵያ እግር ኳስ ደንብ በመጣስ ያልተገቡ ተጨዋቾች በማሰለፍ በተጨማሪም ወደማይመለከተው መደበኛ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመውሰድ ከተጠያቂነት ለማመለጥ ሙከራ በማድረጋቸው እና በኢትዮጵያ ዋንጫ በማጫወታቸው በህገወጥ መንገድ ዋንጫውን በመወሰዳቸው አግባብ አለመሆኑን ተረድቶ ፌዴሬሽኑ ዋንጫውን እንዲመልስ እንጠይቃለን ሲልም ክለቡ ጠይቋል።
በመጨረሻም በነዚህ ጉዳዮች ላይ ፌዴሬሽኑ ውሳኔ ማይሰጥ ከሆን እስከ ዓለም አቀፍ የስፖርቱ ፍርድ ቤት እንደሚወስደው ክለቡ አሳስቧል።


