ከመቐለ 70 እንደርታ ጋር የተለያየው ፈጣኑ የመስመር አጥቂ ማረፊያው ታውቋል።
በሰሞኑ ዘገባዬ ኪቲካ ጀማ በመቐለ 70 እንደርታ የሁለት ደመወዝ አልተከፈለኝም በሚል ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ቅሬታውን ማሳማቱን በኋላም መልቀቂያ ከፌድሬሽኑ ማግኘቱን ተከትሎ ቡድኑን እንደለቀቀም ጭምር ተናግሬ ነበር። በኋላም የመስመር አጥቂው ሀዋሳ ከተማን ለመቀላቀል ድርድር ማድረግ ቢችልም የተሻለ ክፍያን በመሐል በድንገት ገብቶ ነገሌ አርሲ በማቅረቡ የግሉ አድርጎታል።
መቐለ 70 እንደርታ በክረምቱ የተቀላቀለው ክለቡን የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ፣ ገላን ከተማ ፣ ኢትዮጵያ መድን እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋች ለመቐለ የአንድ አመት ውል ፈርሞ በክለቡ ላለፉት ስድስት ወራቶች መቆየት የቻለ ቢሆንም ክለቡን ለቆ ቀጣይ ማረፊያው ነገሌ ሆኗል።
አስተያየት ይስጡ