የዝውውር ዜና
ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አሰልጣኝ መሰረት ማኔን መስፈረም የቻሉት መቻሎች አራት አዳዳሲ ተጨዋቾች ወደ ቡድኑ ቀላቅለዋል በተጨማሪ አንድ ተጨዋች ውል አድሷል ።
የመጀመሪያ ፈራሚ መሆን የቻለችው በ ብራኑ ግዛው ባንክ ቤት ቆይታ ማድረግ የቻለችው የአጥቂ ስፍራ ቦታዋ ተጨዋቿ ትንቢት ሳሙኤል ስትሆን በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከላካይ ስፍራ ስትጫወት የነበረችው ድርሻዬ መንዛ መቻልን ተቀላቅላለች ። ሶስተኛ እና አመለ ሸጋዋ የቀድሞ አሰልጣኟን በመከተል ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወደ መቻል ያቀናችው እፀገነት ቡዛየሁ ናት ።
በሀዋሳ ቤት ጥሩ ቆይታ ማድረግ የቻለችው እና በግሏም እንደቡድን ከሀዋሳ ከተማ ጋር አሪፍ ዓመት ያሳለፈችው ግብጠባቂዋ ቤቴልሄም ዮሀንስ መቻልን መቀላቀል ችላለች ።
በቡድኑ ለመቆየት ለተጨማሪ ዓመት ውሏን ያደሰችው ገነት ሀይሉ ናት አሰልጣኝ መሰረት ማኔ በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ተጨዋቾች ወደ ስብስቧ እንደምትቀላቅል ይጠበቃል።
- ማሰታውቂያ -



