ከሱዳኑ አል ሒላል ጋር በቅርቡ የተለያየው አዲስ ወርቁ የታንዛኒያው አዛም ክለብ ምክትል አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል።
ክለቡ ይፋ ባደረገው የአዲስ ወርቁ ሹመት መሰረት ለአንድ አመት ያህል የክለቡ ምክትል አሰልጣኝ ለመሆን ፊርማውን አኑራል።
አዲስ ወርቁ በአል ሒላል አብሮት ከሰራው ዋና አሰልጣኙ ፍሎረንት ኢቤንጌ ጋር ዳግም በታንዛኒያው ክለብ አብሮ የሚሰራ ይሆናል።
አዛም በ2025/26 የውድድር ዘመን በአፍሪካ የኮንፌዴሬሽኑ ዋንጫ ላይ ተሳታፊ ነው።
- ማሰታውቂያ -



