በዘንድሮ ዓመት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ የተቀላቀለው ሸገር ከተማ የሴቶች ቡድን የድሬዳዋ እና የሉሲዎቹ ግብ ጠባቂ የነበረችውን ሮማን አምባዬ ለአንድ ዓመት በሚቆይ ውል ማስፈረም ችሏል ። ሮማን በ ኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ አራት ዓመት በመሰልጠን ያለፈውን ዓመት በ ቦሌ /ክፍለ ከተማ ጥሩ እንቅስቃሴ ማደረግ ችላለች ። ሸገር ከተማ በ አሰልጣኝ ድሪባ እየተመራ በዛሬው እለት ወደ ዝውውሩ መግባት የቻለ ሲሆን የተለያዪ ዝውውሮችን ይፈፅማል ተብሎ ይጠበቃል ።



