መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዱስ ጊዮርጊስና ማታሲ ሊለያዩ ይሆን?
ቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስና ማታሲ ሊለያዩ ይሆን?

አጋራ
አጋራ

 

” እኔ ትልቅ ተጫዋች ነኝ የትም ሄጄ መጫወት እችላለው ” ፓትሪክ ማታሲ

” በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ታሪክ ውስጥ የውጭ ሀገር ተጫዋች እንደ ማታሲ የታገስነው የለም ” አቶ ዳዊት ውብሸት የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ አባል

 

በፈረሰኞቹ ቤት ያለፉትን አመታት ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ በመሆን ያሳለፈው ፓትሪክ ማታሲ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ከ ሸገር ደርቢው የቀይ ካርድ በኋላ የውሀ ሽታ ሆኖ ከዋናው የቡድን ስብስብ እርቆ ይገኛል ።

ከአመታት በፊት ፈረሰኞቹን መቀላቀል የቻለው የኬንያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ፓትሪክ ማታሲ በክለቡ መጉላላት እየደረሰበት እንዳለ ከ ሀትሪክ ስፖርት ጋር በነበረው ቆይታም ገልጿል በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በኩል ተጫዋቾች ላነሳው ቅሬታ የክለቡ የቦርድ አባል አቶ ዳዊት ውብሸትንም ምላሽ አካተናል።

ከ ሀትሪክ ስፖርት ፀሀፊ ቅዱስ ዮፍታሔ ጋር ቆይታን ያደረገው ፓትሪክ ማታሲ ከ ክለቡ ጋር ስላለው ወቅታዊ ጉዳዮች ሀሳቡን አጋርቶናል ።

” ሶሰት እና አራት ጉዳዮችን ማንሳትን እወዳለው ፣ በመጀመሪያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ጋር ያለኝ ግንኙነት በአሁን ሰዓት ጥሩ አይደለም ። ምክንያቱ እንደሚመስለኝ ከሸገር ደርቢው የቀይ ካርድ በኋላ ብዙ ነገሮች በ ቡድኑ ውስጥ እኔን በተመለከተ እንደ ከዚህ ቀደሙ አይደሉም ።

ቡድኑ ከጅማ የሊጉ ጨዋታዎች ቆይታ ሲመለስ ደብረዘይት ወደ ሚገኘው ካምፕ ካቀና በኋላ ወደ ባህር ዳር ከመጓዛችን አስቀድሞ ለክለቡ ይፋዊ አመራሮች ደብዳቤ አስገብቼ ነበር ፣ ባስገባሁት ደብዳቤም ኮንትራቴን በማቋረጥ ከ ክለቡ ጋር መለያየትን እንደምፈልግ አሳውቄያቸዋለሁ ። ምክንያቱም ከ ክለቡ ጋር ያለኝ ግንኙነት ጥሩ ካለመሆኑም ባሸገር እንደ ክለቡ አንድ የቡድን አባል እየታየሁም አልገኝም ነበር ።አሰልጣኙም ቢሆን እኔን ለማሰለፍ ፍላጎት አልነበረውም ፣ ለዚህም ኮንትራቴን ለማቋረጥ መገደዴን አሳውቄያቸዋለሁ ።

ለክለቡ የመልቀቂያ ደብዳቤ ካስገባሁ በኋላ ክለቡ ሊለቀኝ ፈቃደኛ አመሆናቸውን እና ኮንትራቴን መሰረዝ እንደማይፈልጉ ገልፀውልኛል ። ከዚህ በተቃራኒው ደብዳቤ ሲፅፉልኝ ለሁለት ሳምንታት ወደ ሀገሬ እንድመለስ እና አጋጥሞኝ የነበረውን የቤተሰብ ችግር እንድፈታ ፈቃድ ሰጥተውኝ ነበር ። ይህም ሊሆን የቻለው የእኔን ስልክ ሊያነሱም ሆነ ሊያናግሩኝ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ጠበቃዬ የላከላቸውን መልዕክት ተከትሎ ነበር ። ሆኖም ግን ለአንድ ሳምንታት ብቻ ( ሰኞ እለት ወደ ኬንያ ሄጄ በሳምንቱ ማክሰኞ ) ብቻ ቆይቼ ተመልሰሻለው ።

ከ ኬንያ እንደተመለስኩኝ ለ ክለቡ ከፍተኛ አመራር በተደጋጋሚ ስደውል መልእክቶችን ብልክም እነርሱም ሆኑ የቡድን መሪዎቹ በተመሳሳይ መልእክቶቼን እና የስልክ ጥሪዎቼን አይመልሱም ነበር ።

በመጨረሻም ከዚህ ሁሉ ጊዜያት በኋላ ማግኘት የቻልኩት አቶ ሰለሞንን ሲሆን ከቀናት በፊት ቡድኑ አርብ ከመጫወት በፊት ዕሮብ ጠዋት ላይ ነበር እናም አዲስ አበባ ሆኜ ቡድኑን እንድጠባበቅ ተገልፆልኛል ።

በቤተሰብ ምክንያት ወደ ኬንያ ባቀናሁበት ሰዓት ቡድኑ ሌላ ግብ ጠባቂ ለሙከራ ለማምጣት ወሰነ ፣ ግብ ጠባቂው ለሙከራ እንደመጣ ነግረውኛል ። የእኔ ጥያቄ ግን የነበረው ከ ዩጋንዳ ሌላ ግብ ጠባቂ ከመጣ የእኔ ሚና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ምንድነው የሚል ነበር ። ይሄም የሚያሳየው እነርሱ የእኔን ግልጋሎት እንደማይፈልጉ እና መጠናቀቁን ነው ። ለክለቡ ከፍተኛ ሀላፊዎችም የነገርኳቸው ነገር መልቀቂያን ሰጥተው እኔ ሄጄ አዲሱን ለሙከራ የመጣውን ግብ ጠባቂ ማስፈርም እንደሚችሉ ነው ። ነገሮችን ወደ ህግ ቦታ ወደ ጠበቃዬ ፣ ካፍ እና ፊፋ መውሰድን አልፈልግም ፣ የእኔን አገልግሎት ስላልፈለጉ ሌላ ግብ ጠባቂ አምጠተዋል ፣ የምፈልገው እና የነገርኳቸውም እንዲለቁኝ ብቻ ነው ።

አሁንም የምገኘው በአዲስ አበባ በሚገኘው የክለቡ መኖሪያ ቤት ነው ፣ አሁን እየጠበኩኝ ያለው የኬንያ ብሔራዊ ቡድን ነው ፣ የብሔራዊ ቡድን ጥሪ ቀርቦልኛል ከፊታችን ትልቅ ጨዋታ ይጠብቀናል ። ከግብፅ ብሔራዊ ቡድን ጋር በ ኬንያ ከባድ ጨዋታ አለብን ፣ ከዚህ ጨዋታ በመቀጠል ደግሞ ከ ቶጎ ብሄራዊ ቡድን ጋር እንጫወታለን ። ለእኔ ይሄ ትልቅ አጋጣሚ ነው ፣ በብሔራዊ ቡድን ተሰልፌ በመጫወት ራሴን የማሳይበት ትልቅ የውድድር መድረክ ነው ።

አዲስ አበባ የምጠበቀው የክለቡን ምላሽ ብቻ ነው ያናገረኝም አካል የለም ። ከ አቶ ዳዊት ውብሸት ከቀናት በፊት መልዕክት የተላከለኝ ሲሆን ኮንትራቴ ያላለቀ መሆኑን የሚገለፅ ፅሁፍ ልከውልኛል ። የእኔ ትልቁ ጥያቄ ግን ለምን የፅሁፍ መልዕክት ብቻ እንደሚልኩልኝ ነው ፣ ከዚህም ባለፈ ደውለው በአካል ሊያናግሩኝም አይፈልጉም ። ሁሌም የሚያደርጉት የፁሁፍ መልዕክት ብቻ መላክ ነው ፣ ይህ ደግሞ ጥሩ አይደለም ። እኔ የምፈልገው እነሱ ግልፅ እንዲሆኑ ነው ፣ እንለቅሀለንም አንለቅህም በግልፅ እያሉኝ አይገኙም ፣ እኔ ትልቅ ተጫዋች ነኝ የትም ሄጄ መጫወት እችላለው ።

ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች መናገር የምፈልገው ነገር ክለቡ ምንም ያለኝ ነገር የለም ፣ ደጋፊዎች ወደ ሜዳ በመመለስ ቡድኑን እንዳገለግል ይፈልጋሉ ። ሆኖም ግን አንድም የክለቡ ይፋዊ አመራር ደውሎ ቁጭ ብለን እናውራ ብሎ ወደ ቢሮ የጠራኝ አካል የለም ።

እኔ አሁንም ለቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ልዩ ፍቅር አለኝ ደጋፊውም ከ እኔ ጎን ነበር ፣ እነዚህ ችግሮች ቡድኑ ወደ ድሬደዋ ከማቅናቱ በፊት መፈታት አለባቸው ። በ ቡድኑ ውስጥ አሁንም የምካተት ከሆነ ቡድኑ መድረስ ያለበት ደረጃ ለማድረስ ዝግጁ ነኝ ካልሆነ ግን ሊለቁኝ የሚያስቡ ከሆነ አሁኑኑ ሊለቁኝ ይገባል ሲል ፓትሪክ ማታሲ ስላለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሀሳቡን አካፍሎናል ።

” በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ታሪክ ውስጥ የውጭ ሀገር ተጫዋች እንደ ማታሲ የታገስነው የለም ”

አቶ ዳዊት ውብሸት የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ አባል

ተጫዋቹ የአቋም መውረድ ችግር አለበት ይህም በግልፅ በቴሌቪዥን የሚታይ ነው ፣ መልቀቂያ አንድ ተጫዋች ስላስገባ ብቻ ዝም ብለን አንለቅም ። ቅዱስ ጊዮርጊስ የክለቡን መመሪያ ተከትሎ በ ቦርድ ስብስባ ላይ የተለያዩ ውሳኔዎችን የሚያስተላልፍ ይሆናል ።

ከሳምንታት በፊት የወላጅ እናቱን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰብአዊነት ይቀድማል በሚል ክለቡ ሙሉ የአየር ቲኬት ወጪውን ሸፍኖ ወደ ሀገሩ እንዲሄድ አድርጓል ። በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ታሪክ ውስጥ እንደ ማታሲ የታግሰነው የውጭ ሀገር ተጫዋች የለም ፣ ከዚህ ቀደመም በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ሀገሩ ለመሄድ ቤተሰባዊ ምክንያቶችን ሲያስቀምጥ ቆይቷል ። ማታሲ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ ቡድኑም ሆነ የክለቡ አመራሮች ባህር ዳር ላይ ስለነበሩ ተቀምጠን ለመነጋገር አልተቻለም ። ማታሲን በምንችለው መንገድ ደግፈናል ማንም ሰው እኔንም ጨምሮ ግን ከጊዮርጊስ በታች ነው ።

ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁን ላይ ያሉበትን ክፍተቶች ለመሙላት እና በቀጣይ ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ ክፍተት የሚታይባቸውን ቦታዎች ለመሙላት እየሰራ ይገኛል ። በግብ ጠባቂ ቦታ ላይ ብቻ ሳይሆን በተለያየቱ ቦታዎች ያለቡንን ክፍተቶች ለመሙላት እየሰራን እንገኛለን ። ለምሳሌ በግራ ተመላላሽ ቦታ ላይ ዩጋንዳዊ ተጫዋች አምጥተን ሙከራ ላይ ነበር ፣ የሙከራ ጊዜውን ማለፈ ስላልቻለ ወደ ሀገሩ ሸንተነዋል ።

በአካል አናናግረም ያለው አካል የለም እኔ እና አቶ አብነት ገብረ መስቀል አብረን ሆነን ማስተካከል ስለሚገቡት ነገሮች ተመካክረናል ከዚህ በተጨማሪም ከ አንዴም ሶስቴ ከሌሎች የክለቡ አካላት ጋር ተቀምጠን ለመነጋገር ችለናል ።

የክለቡ ቦርድ በመጪው ቀናት አጠቃላይ የቦርድ ስብሰባ እና ግምገማ ስለሚያካሂድ የማታሲ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ሌሎች የፀባይ ግድፈት ያሳዩ ተጫዋቾችን የምንመረምርበት እና ውሳኔዎችን የምናስተላልፍበት ጊዜያት ይሆናል ።

ከባህር ዳር ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ ከ ቡድን ተጫዋቾቹ ጋር ምሽቱን ተገናኝተን ስላሉት ነገሮች ተነጋግረን አበረታተን ሸኝተናል ። ከፊታችን ሶስት ሳምንት የእረፍት ጊዜ መኖሩ የተለያዩ ችግሮቻችንን እንድንፈትሽ ይረዳናል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...