መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ የፈረሰኞቹ የሰላም ውይይት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል…..
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የፈረሰኞቹ የሰላም ውይይት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል…..

አጋራ
አጋራ

… ከሳሹ ወገን ዛሬ ቦርዱ ሃላፊነቱን መልቀቁን በይፋ ማሳወቅ አለበት እያለ ነው ….

*…. ሌላው ወገን የቦርዱ መልቀቅ በጠቅላላ ጉባኤ የሚወሰን እንጂ አሁን የሚለቅ የለም እያሉ ነው …

 

ቅዱስ ጊዮርጊስ ውስጥ ተፈጥሮ የነበረውን ልዩነት በሰላም የመፍታት ጉዞ ሳንካ ገጠመው።

ከታማኝ ምኔጭ በተገኘ መረጃ ቦርዱ ስልጣኑን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ይሆናል ሲባል እሰከዚህ ዘገባ ድረስ ዝምታን መርጧል። ቦርዱ ዛሬ ስህጣኑን መልቀቁን ሊያሳውቅ ነገ አራት ሰአት በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊዎችና 8 ተወያዮች ከሁለት ሼማግሌዎች ጋር ሊወያዩ በጁፒተር ሆቴል በፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ የተያዘው ቀጠሮ መያዙ እና መጋቢት 21/2018 ባለው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ከሳሹ ወገን ክሱን ሊያነሳ ታስቦ የነበረ ቢሆንም የመሳካቱ ነገር አጠራጣሪ ሆኗል።

ዘገባውን እስካጠናከርንበት ሰአት ድረስ ቦርዱ ዝምታን በመምረጡ የተያዘው ውይይት ላይካሄድ እንደሚችልና የተያዘው የፍርድ ቤቱ ክስ እንደሚቀጥል መረጃዎች ይገልጻሉ።

ቦርዱን በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ አብነት ገ/መስቀል ከውይይቱ በኋላ ሃላፊነታቸውን ማስረከባቸው የፈጠረው ብርሃን ዳግም ችግር ገጥሞታል።

በቦርዱ ወገን ያሉ ወገኖች ግን ዛሬ የሚለቅ የቦርድ አባል እንደሌለ እስከ ጠቅላላ ጉባኤ ድረስ በስራው ላይ እንደሚቀጥልና አቶ ንዋይ በየነ በቼክ ፈራሚነታቸወ እንደሚቀጥሉ የነገው ውይይት የመፍትሄ ማፈላለግና ቀጣይ ስራ ላይ የሚደረግ ስብሰባ ነው ሲሉ ይገልጻሉ።

ሁሉም ወገኖች ታሪካዋውን ክለብ ለማዳነ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመፍትህው አካል እኔዲሆኑ ብዙሃኑ ደጋፊ ጠይቆ አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ የሚለው እሳቤ እንዲተገበር አሳስቧል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...