*….. የኮሚሽነሯ ሪፖርት ይጠበቃል….
አወዛጋቢ የዳኝነት ውሳኔዎች የታዩበት የሲዳማ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ የዳኝነት ውሳኔ ዛሬ ይጠበቃል።
በፕሪሚየር ሊጉ 8ኛ ሳምንት መርሃግብር ባለፈው ሰኞ የሲዳማ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ተካሂዶ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ ይታወቃል። በጨዋታው ሂደት በ44ኛው ደቂቃ ላይ በተገኑ ተሾመ.ላይ የተሰራው ፋውል ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ነው በማለት የዕለቱ የመሃል ዳኛ ኢንተርያሽናል አርቢትር ኤፍሬም ደበሌና ረዳቱ ፌዴራል ረዳት ዳኛ ሚፍታ ሁሴን ውሳኔያቸው ቅጣት ምት መሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል።
የቪዲዮ ምስሎች እንደታየው ጥፋቱ የተሰራው የፍጹም ቅጣት ክልል ውስጥ በመሆኑ ተበድለናል በማለት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ለውድድርና ስነርርዓት ኮሚቴ ክስ መስርተዋል። በእስካሁኑ ሂደት የዳኞቹ ሪፖርት የተላከ ሲሆን የኮሚሽነሯ ፍቅረ ገነት አስማማው ሪፖርትም ከቆይታ በኋላና ለዎድድና ስነስርዓት ኮሚቴው በመግባቱ ዛሬ የሚደረገው ስብሰባ ላይ ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
- ማሰታውቂያ -
ኮሚሽነሯ ፍቅረገነት የዛሬ አመት ተመሳሳይ ክስተት ገጥሟት በትክክለኛ ሪፖርቷ ፌዴራል አርቢትር ባህሩ ተካ መቀጣቱ ይታወሳል። አሁን ግን በእውነተኛ ሪፖርቷ እውነቱን እንዳይጻፍ ሙከራ ተደርጓል የሚል መረጃ በመውጣቱ ውሳኔው እሰኪታወቅ ጉዳዩ ትኩረት አግኝቷል።
ኮሚሽነሯ እውነተኛ ራፖርት ካቀረበች ከፈረሰኞቹ ክስ ጋር ተያይዞ አርቢትሩና ረዳቱ ሊቀጡ እንደሚችሉ የኮሚሽነሩ ሪፖርት ግን በተቃራኒው ከሆነ አርቢትሮቹ ሳይቀጡ ሊግ ኩባንያውው ኮሚሽነሯ ላይ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይገመታል።


