በፕሪሚየር ሊጉ ጅማሮ ውጤታማ መሆን ያልቻለው ሲዳማ ቡና አሰልጣኙን ወንድማገኝ ተሾመን ከባህርዳር ወደ ሀዋሳ እንዲመለስ ማዘዙ ተሰማ።
ከውስጥ አዋቂ በተገኘ መረጃ ሲዳማ ቡናዎች ከድሬዳዋ ከተማ 2ለ2 ተለያይተው በሀድያ ሆሳዕና 4ለ1 በፈረሰኞቹ 5ለ1 ተረትተው 11 ግብ ተቆጥሮባቸው 4 ግብ ብቻ አስቆጥረው ማግኘት ካለባቸው 9 ነጥብ 1 ነጥብ ብቻ ማሳካታቸው በዝውውሩ በከፍተኛ ሁኔታ ለተሳተፉት የሲዳማ ቡና አመራሮች የሚዋጥ አልሆነም።
ክለቡ አሰልጣኙና ቡድን መሪውን ወደሀዋሳ እንዲመለሱ ከማዘዙ ውጪ ጥሪው ለስንብት ይሁን ለምክክር አልታወቀም በቀጣዩ ሀሙስ ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ሲጫወቱ አሰልጣኙ ወንድማገኝ ይሁን አዲስ አሰልጣኝ የታወቀ ነገርም የለም
የሲዳማ ቡና ቦርድም ለነገ 8 ሰዓት ስብሰባ መጥራቱ ታውቋል።
- ማሰታውቂያ -
በፕሪሚየር ሊጉ ቀጣይ ጨዋታዎች የሚሰናበቱና የሚተኩ አሰልጣኞች እነማን ይሆኑ? የሚለው የብዙሃኑን የስፖርት ቤተሰብ ትኩረት የሳበ ሆኗል።