By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: በሳምንቱ የመዝጊያ ጨዋታ አዳማ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሲዳማ ቡናአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባሻሸመኔ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎች

በሳምንቱ የመዝጊያ ጨዋታ አዳማ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አምስተኛዉ ሳምንት የመጨረሻ ዕለት ቀዳሚ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሲዳማ ቡናን 2ለ1 ማሸነፍ ችሏል።

በከፍተኛ ዝናብ ታጅቦ ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ ገና በመባቻዉ በ2ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ተቆጥሯል። በዚህም ጀሚል ያዕቆብ ያቀበለዉን ኳስ አማካዩ መስዑድ መሐመድ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ገና በጊዜ ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ በእንቅስቃሴ ረገድ የተሻሉ የነበሩት ሲዳማ ቡናዎች አደጋ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ተቸግረዉ በተቃራኒው በ20ኛዉ ደቂቃ ላይ ተጨማሪ ግብ አስተናግደዋል።

በዚህም ፍቅሩ አለማየሁ ከግራ መስመር በኩል ወደ ውስጥ ያሻማዉን ኳስ ግብ ጠባቂዉ መክበብ መቆጣጠር አለመቻሉን ተከትሎ ቢኒያም አይተን ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ አድርጓል። ሁለተኛ ግብ ካስተናገዱ በኋላ ወደ ጨዋታዉ ለመመለስ ጥረት ማድረግ የቀጠሉት ሲዳማ ቡናዎች ምንም እንኳን ጥሩ ቢጫወቱም ነገር ግን በሙከራ ረገድ ተዳክመዉ ታይተዋል።

- ማሰታውቂያ -

አጋማሹ ሊጠናቀቅ አንድ ደቂቃ ሲቀረዉ ግን ሲዳማ ቡናዎች ጥረታቸዉ ፍሬ አፍርቶ ወደ ጨዋታዉ የመለሳቸዉን ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም በ44ተኛዉ ደቂቃ ላይ በሳጥኑ ጠርዝ አቡበከር ሻሚል ይገዙ ቦጋለ ላይ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን የቅጣት ምት ኳስ ደስታ ዮሐንስ ወደ ግብነት ቀይሮ አጋማሹ ሁለት ለአንድ ተገባዷል።

ከዕረፍት መልስ በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ቀይረዉ ወደ ሜዳ ያስገቡት ሲዳማ ቡናዎች ወደ ጨዋታዉ የሚመልሳቸውን ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ጥረት ማድረግ የቀጠሉ ሲሆን ነገር ግን አደጋ ለመፍጠር ሲቸገሩ ተስተውሏል። በጨዋታው መሐልም 73ተኛዉ ደቂቃ ላይ የአዳማ ከተማዉ ግብ ጠባቂ ከሳጥን ውጭ ኳስ በዕጅ መንኳቱን ተከትሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።

የአዳማ ከተማዉ ግብ ጠባቂዉ ሰይድ ሀብታሙ ከሜዳ ከወጣ በኋላ ከፍ ባለ ጥረት የማጥቃት ሀይላቸዉን የቀጠሉት ሲዳማ ቡናዎች ዉጥናቸዉ ሰምሮ ተጨማሪ ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ 2ለ1 በሆነ ዉጤት ተሸንፈዋል።

ኢትዮጵያ ቡና ሻሸመኔ ከተማን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል !!

ምሽት 12:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ ፊሽካ በጀመረዉ ጨዋታ አጀማመሩ ላይ ተመጣጣኝ የሜዳ ላይ ፉክክር እየተደረገበት የጀመረ ሲሆን ገና በ18ተኛዉ ደቂቃ ላይ ቡናማዎቹ ሙከራ ማድረግ ችሏል። በዚህም ብሩክ በየነ ከአብዱልከሪም ወርቁ የተቀበለዉን ኳስ ከሳጥን ውጭ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ግብ ጠባቂዉ ኬን ሰይዲ መልሶበታል።

ከተመጣጣኝ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በዘለለ ይህ ነዉ የሚባል ተጠቃሽ ሙከራ እምብዛም ባልተመለከትንበት አጋማሹ በ25ተኛዉ ደቂቃ ላይ የሻሸመኔ ከተማዉ የቀኝ መስመር ተመላላሽ ማይክል ኔልሰን ለማሻማት በሚል በቀጥታ ወደ ግብ የላከዉ ኳስን ግብ ጠባቂዉ በረከት አማረ እንደምንም አውጥቶታል።

በቀሪ የአጋማሹ ደቂቃዎች ተጨማሪ ሙከራ ሳንመለከትበት አጋማሹ የተገባደደ ሲሆን ከዕረፍት መልስ በ52ተኛዉ ደቂቃ ላይ አማካዩ አማኑኤል ዮሐንስ ከሳጥን ዉጭ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሱ በግቡ አናት ላይ ወደ ዉጭ ወጥቷል። በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ኢዮብ ገ/ማርያም ከግራ መሰመር በኩል ያቀበለዉን ኳስ አጥቂዉ ሁዛፍ አሊ ከበረኛ ጋር ተገናኝቶ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ በ72ተኛዉ ደቂቃ ላይ በፍቃዱ አለማዩ ከመስፍን ታፈሰ ጋር ተቀባብሎ ያገኘዉን ኳስ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል። ከግቧ መቆጠር ከሁለት ደቂቃ በኋላ ግን የሻሸመኔ ከተማዉ ሁዛፍ አሊ ከተከላካዩ ራምኬል ጀምስ ታግሎ ያገኘዉን ኳስ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ አድርጓል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ መደበኛዉ ዘጠና ደቂቃ ተጠናቆ በተጨመረ ደቂቃ በ90+1 ቡናማዎቹ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም አብዱልከሪም ያሻገረዉን የቅጣት ምት ኳስ ተከላካዩ ራምኬል ጀምስ በግንባሩ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አሸናፊ ማድረግ ችሏል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አቻ ሲለያዩ ፥ መቻል ደግሞ ሁለት ጊዜ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!
Next Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ አምስተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ኢትዮ-ኤሌክትሪክየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በነገው እለት በኢትዮ ኤሌክትሪክ በይፋ ሰራቸውን ይጀምራሉ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
አንበሳ ቢራ አዳማ ከተማ እግር ኳስ ክለብን ስፖንሰር ለማድረግ ተስማማ
“ያለ ኢት.ቡና ደጋፊ ጨዋታን ማድረግ ለእኔ ከወዲሁ ከባድ ሆኖብኛል” አቡበከር ናስር
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለሴካፋ ሻምፒዮና ዛሬ 10 ሰዓት ሩዋንዳን ይገጥማል
በ44ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፕዮና ኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀች
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?