By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አቻ ሲለያዩ ፥ መቻል ደግሞ ሁለት ጊዜ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
መቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሀዋሳ ከተማሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባ

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አቻ ሲለያዩ ፥ መቻል ደግሞ ሁለት ጊዜ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አምስተኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ሶስተኛ ዕለት ጨዋታ የተገናኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት ደምድመዋል።

በጨዋታዉ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የወሰዱት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በ13ተኛዉ ደቂቃ ላይ በይገኑ ተሾመ ሙከራ ማድረግ የቻሉት ፈረሰኞቹ በ17ተኛዉ ደቂቃ መሪ መሆን የቻሉበትን ግን ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም አማኑኤል ኤረቦ ለበረከት ወልዴ ያቀበለዉን ኳስ ተጫዋቹ ወደ ግብነት መቀየር ይሏል።

ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ የአቻነት ግብ ለማስቆጠር ለመንቀሳቀስ የጀመሩት ሀድያዎች በመጀመሪያው አጋማሽ በተመስገን ብርሐኑ እና ፀጋዓብ ግዛዉ አማካኝነት በ24ተኛዉ እና 30ኛዉ ደቂቃ ላይ ሁለት ሶስት ተጠቃሽ ሙከራ ቢያደርጉም ግብ ማርቆጠር ሳይችሉ አጋማሹ በፈረሸኞቹ መሪነት ተገባዷል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ሁለት ተጫዋቾችን ቀይሮ ወደ ሜዳ ያስገባዉ ሀድያ ሆሳዕና በ65ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ለማስቆጠር ተቃርቦ ነበር ፤ በዚህም ከቀኝ መስመር በኩል በረከት ወ/ዮሐንስ ያሻገረዉን ኳስ ተስገን ብርሀኑ በጭንቅላቱ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ወጥታለች።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ ተቀይሮ የገባዉ በየነ ባንጃዉ ያቀበለዉን ኳስ ሳሙኤል ዮሐንስ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የግቡ ቋሚ ከመለሰዉ በኋላ ኳሷን ያገኘዉ ዑመድ ዑክሪ ወደ ግብነት ቀይሯል። በቀሪ ጨዋታዎች ሁለቱም ክለቦች ተመጣጣኝ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ አድርገዉ ጨዋታቸዉን አንድ አቻ አጠናቀዋል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ መቻል ሀዋሳ ከተማን በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

ምሽት 12:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ አሸብር ሰቦቃ መሪነት በጀመረዉ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች ላይ በተመጣጣኝ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ መርሐግብራቸዉን የጀመሩ ሲሆን ፤ አጀማራቸዉ የተሻለ የነበሩት መቻሎም ቀዳሚ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በዚህም በ5ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከግራ መስመር በኩል ሽመልስ በቀለ ያሻገረለትን ኳስ ከንዓን ማርክነህ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ግን ለጥቂት በግቡ ቋሚ አጠገብ ወጥታለች።

በአብዝኛዉ ደቂቃ ጨዋታዉን ለመቆጣጠር የተቸገሩት ሀይቆቹ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በ14ተኛዉ ደቂቃ ላይ መቻልች በራሳቸዉ የሜዳ ክፍል ላይ በኳስ ቅብብል ወቅት የሰሩትን የቅብብል ስህተት ተከትሎ ኳሱን ያገኘዉ አጥቂዉ አሊ ሱለይማን ከሳጥን ውጭ አስደናቂ ግብ አስቆጥሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ሲችል ለራሱም አስራ አተኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።

በ25ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከግራ መስመር በኩል ሽመልስ በቀለ ያሻማዉን ኳስ ተከላካዮች ሲመልሱት ያገኘዉ ከንዓን ኳሷን ሲጨርፋት ያገኛት ምንይሉ ወንድሙ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ አዉጥቷታል።

ከግቧ መቆጠር በኋላ የአቻነት ግብ ፍለጋ መታተር የቀጠሉት መቻሎች ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም በ35ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከኋላ ክፍል የተሻገረዉን ኳስ የተቆጣጠረው ሽመልስ በቀለ አጠገቡ ለሚገኘዉ ከንዓን ማርክነህ አቀብሎት ተጫዋቹም ከሀዋሳ ከተማ ተከላካዮች ጋር ታግሎ ኳስ የቻርልስ ሉክዋጎ መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ አጋማሹ ሊጠናቀቅ ሶስት ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩት ሀይቆቹ ሶስተኛ ግብ በአሊ ሱለይማን አማካኝነት ለማስቆጠር ተቃርበዉ የነበረ ቢሆንም የግቡ ቋሚ ግን ከልክሏቸዉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት መልስ በ59ነኛዉ ደቂቃ ላይ አሊ ሱለይማን ላይ የቻሉ ተከላካይ ነስረዲን ሀይሉ ጥፋት መስራቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት ራሱ አሊ ሱለይማን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን ዳጎሚ መሪ ማድረግ ችሏል።

የአቻነት ግብ ለማስቆጠር ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት መቻሎች በ69ነኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ከቀኝ መስመር በኩል የተሻገረዉን ኳስ ተከላካዮች ተደርበዉ ሲመልሱት በቅርብ ርቀት ኳሷን ከሳጥን ውጭ ያገኘዉ ከንዓን በቀጥታ ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል።

ወደ ቀኝ መስመር በኩል ጨና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት መቻልች በ79ነኛዉ ደቂቃ ላይ ሶስተኛ ግብ ማግኘት ችለዋል ። በዚህም በተጠቀሰዉ ደቂቃ ከቀኝ መስመር ሳሙኤል ሳሊሶ ያሻማዉን ኳስ ተከላካዮች በሚገባ ማፅዳት ባለመቻላቸዉ ምክንያት ኳሷን አየር ላይ ያገናኛት አብዱ ሞታላቦ በመቀስ ምት ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን ወደ መሪነት ማምጣት ችሏል።

በቀሪ ደቂቃዎች በሁለቱም ክለቦች በኩል አዝናኝ የሜዳ ላይ ፉከክር አስመልክተዉን ጨዋታዉ በመቻል 3ለ2 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ባህርዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸዉን ማሸነፍ ችለዋል !!
Next Article በሳምንቱ የመዝጊያ ጨዋታ አዳማ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ ዉጤት ማሸነፍ ችለዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግዜናዎችኢትዮ-ኤሌክትሪክ

ኢትዮ ኤሌክትሪክ አሰልጣኝ አንዋር ያሲንን አሰናበተ

hatricksport team By hatricksport team 6 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ኢትዮጵያ ቡና በአቡበከር ናስር ሀትሪክ ሸገር ደርቢን በድል ተወጥቷል
ኢትዮጵያ ቡና ከአትዮጵያ መድን ያለውን የነጥብ ልዩነት ያጠበበትን ወሳኝ ድል አሳክቷል
መቐለ 70 እንደርታ አዳማ ሲሴኮን አስፈረመ
ሊግ ካምፓኒና ዲ ኤስ ቲቪ የፊታችን አርብ ይፈራረማሉ!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?