By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ባህርዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸዉን ማሸነፍ ችለዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችድሬዳዋ ከተማባህርዳር ከተማሀምበሪቾ ድራሜ

ባህርዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸዉን ማሸነፍ ችለዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አምስተኛዉ ሳምንት የሊጉ ሁለተኛ ዕለት ቀዳሚ ጨዋታ ባህርዳር ከተማ ሀምበሪቾ ዱራሜን ማሸነፍ ችሏል።

በጨዋታው መባቻ ሀብታሙ ታደሰ ከያብስራ ተስፋየ ጋር አንድ ሁለት ተቀባብሎ ሳጥን ዉስጥ ከደረሰ በኋላ ቺፕ አድርጎ ወደ ግብ በላካት ኳስ ሙከራ ማድረግ የጀመሩት የጣና ሞገዶቹ ጫና ፈጥረዉ መጫወታቸውን ቀጥለዉ በ15ተኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ፀጋየ አበራ ከሀብታሙ ታደሰ በተቀበለዉ ኳስ ከርቀት ድንቅ ሙከራ አድርገዉ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ ፓሉማ ፓጁ አዉጥቶበታል።

በ23ተኛዉ ደቂቃ ላይ በኃይሉ ተሻገርን በጉዳት ምክንያት አስወጥተዉ በፍቃዱ አስረሳኸኝን ቀይረዉ ያስገቡት ሀምበሪቾዎች በተከታታይ በአጥቂዉ ሀብታሙ ታደሰ ሙከራዎች ከተደረገባቸው በኋላ ፤ በ28ተኛዉ ደቂቃ ላይ በአልዓዛር አድማሱ አማካኝነት የመጀመሪያ ሙከራቸዉን ማድረግ ቢችሉም ግብ ጠባቂዉ ፔፔ ሰይዶ ይዞባቸዋል።

- ማሰታውቂያ -

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ አጋማሹ ሊጠናቀቀት በ45+1 ደቂቃ ላይ የጣና ሞገዶቹ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ። በዚህም የመስመር ተጫዋቹ ፍፁም ጥላሁን ከሳጥኑ ዉጭ የመታዉን ኳስ ተከላካዩ ትዕግስቱ አበራ ጨርፎት መረብ ላይ አርፏል።

ሁለተኛዉ አጋማሽ በተመሳሳይ እንቅስቃሴ ቀጥሎ በ50ኛዉ ደቂቃ ላይ ረጀብ ሚፍታህ ከቀኝ በኩል ያሻገረዉን ኳስ ፍፁም ጥላሁን በግንባሩ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ መልሶበታል። በአጋማሹ በተደጋጋሚ በሀብታሙ ታደሰ እና ፍፁም ጥላሁን ሙከራ ማድረግ የቀጠሉት የጣና ሞገዶቹ በ72ተኛዉ ደቂቃ ላይ ተሳክቶላቸዉ ሁለተኛ ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም ከቀኝ በኩል አባይነህ ፌኖ ያሻገረዉን ኳስ ፍፁም ጥላሁን መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል።

በጨዋታዉ ምንም እንኳን በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ተፎካካሪ ይሁኑ እንጅ በሙከራ ረገድ ደካማ የነበሩት ሀምቢቾዎች በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ በአብዱልከሪም ዱግዋ እና አልዓዛር አድማሱ አማካኝነት ሙከራ ማድረግ ቢችሉም በፔፔ ሰይዶ ድንቅ ብቃት ከግብነት ከሽፈዉ ጨዋታዉ በባህርዳር ከተማ 2ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን ከጨዋታ ብልጫ ጋር ድሬዳዋ ከተማን 5ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል ።

አመሻሽ 12:00 ሲል በጀመረዉ ጨዋታ በተሻለ የጨዋታ ብልጫ እንቅስቃሴያቸዉን የጀመሩት ኢትዮጵያ መድኖች ከአንድ ሁለት ኢላማቸዉን ያልጠበቁ ሙከራዎች በኋላ በ17ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። በዚህም ከማዕዘን የተሻማዉን ኳስ የድሬዳዋ ከተማ ተከላካዮች በሚገባ ማፅዳት ባለመቻላቸዉ ምክንያት ኳሱን ያገኘዉ አለን ካይዋ ኳሷን ወደ ግብነት ቀይሮ ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

የመክፈቻዋ ጎል ከተቆጠረች በኋላ በ22ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሀይደር ሸረፋ ከቆመ ኳስ ወደ ዉስጥ ያሻማዉን ኳስ ብሩክ ሙሉጌታ በግንባሩ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ አብዩ ካሳየ እንደምንም አውጥቶበታል። በ29ነኛዉ ደቂቃ ላይ ደግሞ ኳስ በዕጅ መነካቱን ተከትሎ የተሰጠዉን ፍፁም ቅጣት ምት አምበሉ ሀይደር ሸረፋ ወደ ግብነት ቀይሮ የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ አድርጓል።

ሁለት ጎሎች ከተቆጠሩባቸዉ በኋላ ወደ ጨዋታዉ ለመመልስ ጥረት ያደርጉ የነበሩት ድሬዳዋ ከተማዎች በ37ተኛዉ ደቂቃ ላይ መሐመድ አብዱለጢፍ አሻግሮለት ቻርልስ ሙሰጌ በግባሩ ገጭቶት አቡበከር ባወጣዉ ኳስ ኢላማዉን የጠበቀ ሙከራ ማድረግ ችለዋል። በድጋሚ ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ አድናን መኪ ከርቀት ድንቅ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ግብ ጠባቂዉ አቡበከር በሚገርም ብቃት ኳሷን አውጥቷት አጋማሹ ተገቧዷል።

ከዕረፍት መልስ ይበልጥኑ የማጥቃት ሀይላቸዉን አጠናክረዉ የቀጠሉት መድኖቸ በ48ተኛዉ ደቂቃ ላይ አለን ካይዋ ከብሩክ ሙሉጌታ በተቀበለዉ ኳስ ድንቅ ግብ አስቆጥሮ መሪነታቸዉን ወደ ሶስት ከፍ ማድረግ ችሏል። አሁንም ጫና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉት መድኖች በ60ኛዉ ደቂቃ ላይ በጨዋታዉ ላይ ድንቆ ሆኖ ባመሸዉ አለን ካይዋ አማካኝነት አራተኛ ግብ ማስቆጠር ችለዋል ፤ ተጫዋቹም ሀትሪክ መስራት ችሏል።

ድሬዳዋ ከተማዎች አራተኛ ግብ ካስተናገዱ ከአምስት ያክል ደቂቃዎች በኋላ በሱራፌል ጌታቸዉ አማካኝነት ከርቀት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም የግቡ አግዳሚ መልሶባቸዋል። በቀሪ ደቂቃዎች መድኖች በሙሉ የጨዋታ ብልጫ ተንቀሳቅሰዉ በ90+4 ደቂቃ ላይ በብሩክ ሙሉጌታ አማካኝነት ድንቅ ግብ አክለዉ ጨዋታዉ በኢትዮጵያ መድን 5ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

 

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article በፓሪስ ኦሎምፒክ የሚካፈለው የኢትዮጵያ የማራቶን ቡድን ይፋ ተደረገ
Next Article ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አቻ ሲለያዩ ፥ መቻል ደግሞ ሁለት ጊዜ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስቃለመጠይቅ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ማልያ የድል ማልያ ነው ይሄን ማልያ መልበስ የአሸናፊነት ስሜት መላበስ ነው !! ሀብታሙ ጉልላት

fitsum Wadu By fitsum Wadu 8 months ago
ሀትሪክ በቀጠሮዋ ቀን ነገ
    እንደልማድዎ ይጠብቋት….አሁንም ቀጠሮ አክባሪ ናት…
የጨዋታ ዘገባ | መከላከያ በቢንያም በላይ ሁለት ግቦች ወደ አሸናፊነት ተመልሷል
የጨዋታ ዘገባ | የሔኖክ አየለ የመጨረሻ ደቂቃ ግብ ድሬዳዋ ከተማን አንድ ነጥብ አስገኝታለች !!
ሲዳማ ቡና ናይጄሪያዊውን አጥቂ ለማስፈረም ከጫፍ ደርሷል !
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?