By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ ኢትዮጵያ ቡናም ወሳኝ ድል አሳክቷል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችሀዋሳ ከተማሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናወላይታ ድቻ

የሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ ኢትዮጵያ ቡናም ወሳኝ ድል አሳክቷል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በተጠባቂዉ የሮድዋ ደርቢ ሀዋሳ ከተማ ከሲዳማ ቡና ጋር ጨዋታቸውን አንድ አቻ በሆነ ዉጤት አጠናቀዋል።

በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ ቀን 9:00 ሰዓት በዋና ዳኛ ዳንኤል ይታገሱ ፊሽካ በጀመረዉ ጨዋታ እንደጨዋታዉ ተጠባቂነት በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ ጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር በሁለቱም ክለቦች በኩል ተደርጓል። በዚህ ሁነት በጀመረዉ ጨዋታ 16ተኛዉ ደቂቃ ላይም ሀይቆቹ ጨዋታዉን መምራት የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል። በዚህም አጥቂዉ አሊ ሱለይማን ከኋላ ክፍል የተቀበለውን ኳስ ለታፈሰ ሰለሞን አቀብሎት ተጫዋቹም ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን ቀዳሚ አድርጓል።

ግብ ከተቆጠረባቸዉ በኋላ በቶሎ ሪያክት ለማድረግ መጣር የጀመሩት ሲዳማ ቡናዎች በአጥቂዉ ማይክል ኪፕሩል እና አማካኝነት ካደረጓቸዉ ኢላማቸዉን ያልጠበቁ ሙከራዎች ዉጭ አደጋ ለመፍጠር ሲቸገሩ በተቃራኒው አቤኔዘር አስፉዉ ያደረገዉን ተጠቃሽ ሙከራ ግብ ጠባቂዉ ቻርልስ መልሶበታል።

ከዕረፍት መልስ ከመጀመሪያው አጋማሽ በተለየ ተሻሽለዉ ወደ ሜዳ የተመለሱት ሲዳማ ቡናዎች የአቻነት ግብ ፍለጋ ጨና ፈጥረዉ መጫወት የቀጠሉ ሲሆን ፤ ካደረጓቸዉ ሙከራዎች መካከልም በ70ኛዉ ደቂቃ ላይ ብርሀኑ በቀለ ከቅጣት ምት ያሻማዉን ኳስ በዛብህ መለዮ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

- ማሰታውቂያ -

በተቃራኒው ጨዋታዉን በመምራት ላይ የሚገኙት ሀይቆቹ በሁለተኛዉ አጋማሽ በተጋጣሚያቸው ብልጫ ተወስዶባቸዉ የነበረ ሲሆን ይባስኑም በ74ተኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ አስተናግደዋል። በዚህም ከቀኝ በኩል ከማዕዘን ያሻማዉን ኳስ ደስታ ደሙ በግንባር ገጭቶ ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን አቻ ማድረግ ችሏል። በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ሁለቱም ክለቦች ከጨዋታዉ ሙሉ ሶስት ነጥብ ይዘዉ ለመዉጣት ያደረጉት ጥረት ሳይሰምር ቀርቶ ጨዋታዉ 1ለ1 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ኢትዮጵያ ቡና ወላይታ ዲቻን 2ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

አመሻሽ 12:00 ሰዓት ሲል በኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ መሪነት በተጀመረዉ ጨዋታ ቡናማዎቹ በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ ሁነዉ በመቅረብ ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረስ የሚገኙ ዕድሎችንም ለመጠቀም ሲጥሩ ፤ በተቃራኒው ወላይታ ዲቻዎች ደግሞ በአብዛኛው ወደ መስመር ባደላ አጨዋወት ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

በዚህ ሂደት በጀመረዉ ጨዋታም ምንም እንኳን ሁለቱ ክለቦች አዝናኝ በነበረ የጨዋታ እንቅስቃሴ ጥሩ አጀማመር ያድርጉ እንጅ ሁለቱም ክለቦች ተጠቃሽ ሙከራ ለማድረግ ተቸግረዉ በ38ተኛዉ ደቂቃ ላይ ወላይታ ዲቻዎች ጨዋታዉን መምራት የቻሉበትን ግብ አግኝተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ ቡናዉ ተከላካይ ራምኬል የሰራዉን ስህተት ተከትሎ የተገኘዉን ኳስ አበባየዉ ሀጂሶ ለብዙአየሁ አቀብሎት ተጫዋቹም ወደ ግብነት በመቀየር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

ከግቧ መቆጠር ከአራት ያክል ደቂቃዎች በኋላ በድጋሚ አጥቂዉ ቢኒያም ፍቅሬ ድንቅ ሙከራ አድርጎ ፤ በተቃራኒው በኳስ ቁጥጥሩ የተሻለ የነበረዉ ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ ተጠቃሽ ኢላማዉን የጠበቀ ሙከራ ሳያደርግ አጋማሹ ተጠናቋል። ከዕረፍት መልስ የበላይነታቸዉን አጠናክረው የቀጠሉት ቡናማዎቹ በ49ነኛዉ ደቂቃ ላይ የአቻነት ግብ አግኝተዋል። በዚህም አብዱልከሪም ወርቁ ያሻማውን የማዕዘን ኳስ መስፍን ታፈሰ በግንባሩ ወደ ግብነት መቀየር ችሏል።

በ73ተኛዉ ደቂቃ ላይ ናትናኤል ናሲሮን በቀይ ካርድ ምክንያት ከሜዳ ካጡ በኋላ ጨናዉ የበረታባቸዉ ዲቻዎች ይባስኑ በ84 ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ግብ አስተናግደዋል። በዚህም ከቀኝ መስመር በኩል አብዱልከሪም ወርቁ ያሻገረዉን ኳስ መሐመድ ኑር ናስር በግሩም ሁኔታ ወደ ግቅነት ቀይሯል። በቀሪ ደቂቃዎችም ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠር ጨዋታዉ በኢትዮጵያ ቡና 2ለ1 በሆነ አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ቅዱስ ጊዮርጊስ ለተከታታይ ሶስተኛ ጊዜ ሲሸነፍ ፤ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክም ነጥቡን ወደ ሀምሳ ከፍ ያደረገበትን ድል አስመዝግቧል !!
Next Article ሀድያ ሆሳዕና እና መቻል በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ማሸነፍ ችለዋል !!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ደደቢትየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

የደደቢት ተጨዋቾች ልምምድ አቋርጠዋል

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 7 years ago
የተጨዋቾቻቸውን ደመወዝ የከፈሉ ክለቦች 10 ደረሱ
በረከት አማረ መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቅሏል
ለካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ፍክክር ኢትዮጵያ አቶ ጁነዲን ባሻህ በመጨረሻው ሠዓት ራሳቸውን ከፉክክሩ ዉጪ(ሪዛይን) አርገዋል
ኤፍሬም ኃይለማርያም፣ ግሩም ሃጎስ፣ ብርሃኑ አዳሙ እና ብሩክ እንዳለ የጨዋታ እገዳ ተጣለባቸው
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?