ሀትሪክን በቅዳሜ እትሟ ጠብቋት
የሀትሪክ የፊት ለፊት ገፅ የሚከተለውን ይመስላል
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ በተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ
ዘገባዎቿ ታጅባ ነገ ለንባብ ትቀርብሎታለች።
ሀትሪክ በሀገር ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት ዘ ቢግ
ኢንተርቪው አምድ የጋዜጣው ኤክስኪዩቲቭ ኤዲተርና ጋዜጠኛ
የሆነው ይስሃቅ በላይ ኢትዮጵያ ቡናን በዝውውር መስኮቱ
ከለቀቀው አህመድ ረሺድ ሺሪላ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፋ
ያለ ቆይታን አድርጓል። ምን ብሎ ይሆን? ሀትሪክ ከዛ በተጨማሪም
ከቡና ጋር በተያያዘ በወቅታዊ የክለቡ ጉዳዮች ዙሪያም ከዋናው
ስራ አስኪያጁ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ ጋርም ቆይታን ያደረግን ሲሆን
በሌላ መረጃዎችም ድንገተኛ ጉዳት የደረሰበትን የቅዱስ ጊዮርጊሱን
የአብስራንም በህመሙ ዙሪያ አናግሮት ተጨዋቹ ምላሽን ሰጥቷል።
ሀትሪክ የፋሲል ከነማው የመሀል ሜዳ ተጨዋች የሆነውን
ሀብታሙ ተከስተንም በኳስ ህይወቱ ዙሪያ እና ስለ ቡድኑም
አናግሮት ተጨዋቹ ምላሹን የሰጠ ሲሆን ከዛ ውጪም ሌላ የተለያዩ
መረጃዎችም አላት።
ሀትሪክ በባህር ማዶም የተለያዩ የአውሮፓ ሊጎችን አስመልክተን
በርካታ መረጃዎችን የምትሰጦት ሲሆን በመዝናኛ አምዷም
የሚወዷቸው ዘገባዎችን አቅርባሎታለች።
ሀትሪክ አታምልጦት።
ሀትሪክን በቅዳሜ እትሟ ጠብቋት የሀትሪክ የፊት ለፊት ገፅ የሚከተለውን ይመስላል
Hatricksport team