By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ሀድያ ሆሳዕና እና መቻል በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ማሸነፍ ችለዋል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሀምበሪቾ ድራሜሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባመቻልሻሸመኔ ከተማ

ሀድያ ሆሳዕና እና መቻል በሳምንቱ የመጨረሻ ጨዋታ ማሸነፍ ችለዋል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ አራተኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታ ሀድያ ሻሸመኔ ከተማን 3ለ1 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

ቀን ዘጠኝ ሰዓት ሲል በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በሙከራ ረገድ ቀዳሚ የነበሩተ ሻሸመኔ ከተማዎች በ9ነኛዉ እና በ10ኛዉ ደቂቃ ጥሩ ሙከራዎችን አድርገዋል። በዚህም ሁዛፍ አሊ ከእዮብ ገ/ማርያም የተቀበለዉን ኳስ ከሳጥን ዉጭ በቀጥታ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ኳሷ በግቡ የግራ ቋሚ አጠገብ ለጥቂት ስትወጣ ፤ በተጨማሪም ተከላካዩ ገዛኸኝ ደሳለኝ የቅጣት ምት በተሻማ ኳስም ድንቅ ሙከራን አድርጓል።

በሙከረ ረገድ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሀድያዎች ከቀኝ መስመር በኩል እዮብ ገ/ማርያም ድንቅ ኳስ ለቻላቸዉ አቀብሎት ተጫዋቹም በደካማ ዉሳኔ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ግብ ጠባቂዉ ኳሷን ወደ ውጭ አውጥቷል። በዚህ ሂደት በጀመረዉ ጨዋታ በ19ነኛዉ ደቂቃ ላይ ጎል ተቆጥሯል። በዚህም ተመስገን ብርሀኑ ከመሐል ሜዳ ጀምሮ ያገኛትን ኳስ ግብ ጠባቂዉን አቤልን እና ቻላቸዉን ጭምር አልፎ ጎል በማስቆጠር ክለቡን መሪ ማድረግ ችሏል።

አጋማሹ ሊጠናቀቅ አንድ ደቂቃ ሲቀረዉም ከግራ መስመር በኩል ዳዋ ሁቴሳ ከኋላ የተሻገረለትን ኳስ ከተቆጣጠረ በኀላ ለተመስገን ብርሀኑ አቀብሎት ተጫዋቹም ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር የክለቡን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ ከድርጎ አጋማሹ ተገባዷል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ የተጫዋች ቅያሪ ካደረጉ በኋላ በይበልጥ ረዣዥም ኳሶችን ተጠቅመዉ የግብ ዕድል ለመፍጠር ሲጥሩ የተስተዋሉት ሻሸመኔ ከተማዎች በ55ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከማዕዘን በተሻማ ኳስ ተከላካዩ ገዛኸኝ ግብ አስቆጥሮ ክለቡን ወደ ጨዋታዉ መልሷል። ከግቧ መቆጠር በኋላ በተመስገን ብርሀኑ አማካኝነት ሙከራ ማድረግ የቻሉት ሀድያዎች በ74ተኛዉ ደቂቃ ላይ ሳሙኤል ዮሐንስ ከሳንጥኑ ዉጭ ከርቀት የቀኝ ጠርዝ ድንቅ የግብ ሙከራ ማድረግ ችሎ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኳሷ በግቡ ቋሚ አጠገብ ለጥቂት ወደ ዉጭ ወጥታለች።

በጥሩ መነቃቃት እየቀጠለ በነበረዉ ጨዋታም በ84ተኛዉ ደቂቃ ላይ ከቅጣት ምት የተሻማዉን ኳስ የሻሸመኔ ከተማ ተከላካዮች በሚገባ ማፅዳት ባለመቻላቸው ምክንያት በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘዉ ደስታ ዋሚሾ ኳሷን ወደ ግብነት በመቀየር የሻሸመኔ ከተማዎችን የማንሰራራት ተስፋ አደብዝዞ ጨዋታዉ በሀድያ ሆሳዕና 3ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር መቻል በሽመልስ በቀለ ሁለት ጎሎች ታግዞ ሀምበሪቾ ዱራሜን ማሸነፍ ችሏል።

በዋና ዳኛ ተካልኝ ለማ ፊሽካ 12:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ ጨዋታ መቻሎች ገና በመባቻዉ በ2ተኛዉ ደቂቃ ላይ በሽመልስ በቀለ አማካኝነት ድንቅ ሙከራ ማድረግ ችለዉ የነበረ ቢሆንም ኳሷ ግን ለጥቂት ወደ ውጭ ወጥታለች። ገና በጊዜ ሙከራ በማድረግ ጨዋታዉን የጀመሩት እና በእንቅስቃሴ ረገድም የተሻሉ የነበሩት መቻሎች በ30ኛዉ ደቂቃ ላይ ግብ ለማስቆጠር ተቃርበዉ ነበር በዚህም ከግራ መስመር በኩል በረከት ደስታ ያሻገረዉን ኳስ ያገኘዉ ሽመልስ በቀለ ወደ ግብ ቢሞክርም የግብ ዘቡ ኳሷን ይዞበታል።

በድጋሚ ከሶስት ደቂቃዎች በኋላም ሽመልስ በቀለ ድንቅ የግብ ዕድል አግኝቶ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን በዉሳኔ አሰጣጥ ችግር ጭምር ኳሷን ሳይጠቀምባት ወደ ዉጭ ወጥታለች። በተቃራኒው በአብዛኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ በመከላከል ያሳለፉት እና ከቆሙ ኳሶችም ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ የነበሩት ሀምበሪቾዎች በአጋማሹ አንድም ተጠቃሽ ሙከራ ሳያደርጉ ለዕረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ከዕረፍት በኋላም የማጥቃት ሀይላቸዉን አጠናክረዉ የቀጠሉት መቻሎች በ53ተኛዉ እና በ60ኛዉ ደቂቃ ላይ በተከታታይ ግብ ማስቆጠር ችሏል። በዚህም በመጀመሪያው ደቂቃ ከወደ ግራ በኩል የተገኘዉን የቅጣት ምት ኳስ ወደ ግብነት በቀጥታ መቀየር ሲችል ፤ ከደቂቃዎች በኋላም ከበረከት ደስታ የተቀበለዉን ኳስ ወደ ግብነት ቀይሮ የክለቡን መሪነት ዘደ ሁለት ለዜሮ ከፍ ማድረግ ችሏል።

ግብ ካስቆጠሩ በኋላ በይበልጥ ጨዋታዉን የተቆጣጠሩት መቻሎች በምንይሉ ወንድሙ እና ሽመልስ በቀለ አማካኝነት ተጨማሪ ግቦችን ለማስቆጠር ተቃርበዉ እንዲሁም በ80ኛዉ ደቂቃ ላይ ዳዊት ማሞ ከርቀት ድንቅ ሙከራ አድርጎ የግቡ ቋሚ መልሶበት ጨዋታዉ በመቻል 2ለ0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ ኢትዮጵያ ቡናም ወሳኝ ድል አሳክቷል !!
Next Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ አራተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወልዋሎዜናዎች

የወልዋሎው አምበል ወደ ቀድሞ ክለቡ አቅንቷል.

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
ወላይታ ድቻ ና ዛማሌክ የመጨረሻ ልምምዳቸውን አከናውነዋል
በኘሪሜየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ና ወልዲያ ድል ቀንቷቸዋል
የኢ.እ.ፌ ፕሬዝዳንት ለሰዓታት ቦሌ አየር ማረፊያ ከቆዩት የካፍ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ
ወልቂጤ ከተማ አዳነ ግርማን የግሉ አድርጓል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?