በኢትዮጵያ ዋንጫ ሀዋሳ ከተማ በድሬዳዋ ከተማ ሽንፈት ባስተናገደበት ጨዋታ ላይ የቀይ ካርድ የተመለከተው አማካይ ቅጣት ተጥሎበታል።
በአሰልጣኝ ተመስገን ዳና የሚመሩት ሀዋሳ ከተማዎች በኢትዮጵያ ዋንጫ ጨዋታ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ድሬዳዋ ከተማን አስተናግደው ሬድዋን ሸነፋ ባስቆጠራት ብቸኛ ጎል ተሸንፈው ከውድድሩ ውጪ መሆናቸው ይታወቃል። በጨዋታው ላይ ተሰልፎ መጫወት የቻለው አማካዩ ሽመልስ በቀለ በጨዋታው መሐል ከዕለቱ ዳኛ ዳንኤል ግርማይ ጋር የነበረው የሜዳ ላይ ሰጠገባ ተጫዋቹ ተቀይሮ ከወጣም በኋላ ጉዳዩ ተባብሶ ቀጥሎ ቀጥታ ቀይ ካርድን ተጫዋቹ መመልከቱ ይታወሳል።
ይህንንም ተከትሎ ሪፖርት የቀረበበት ተጫዋቹ በቀጣይ በፕሪምየር ሊጉ ክለቡ በሚያደርጋቸው አራት ጨዋታዎች ላይ መሳተፍ እንዳይችል መቀጣት የቻለ ሲሆን በተጨማሪም የገንዘብ ቅጣትም እንደተጣለበት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።


