መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ ዲሲፕሊን ኮሚቴ የሰበታ ከተማና 21 ተጨዋቾቹ ውዝግብ ላይ ውሳኔ አስተላለፈ
ሰበታ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዲሲፕሊን ኮሚቴ የሰበታ ከተማና 21 ተጨዋቾቹ ውዝግብ ላይ ውሳኔ አስተላለፈ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ 21, የሰበታ ተጨዋቾች የሶስት ወር ደመወዝ አልተከፈለንም የ2013 ውዝፍ ክፍያ አለን ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ውሳኔ ሰጥቷል።

ዛሬ ይፋ በሆነው ውሳኔ ተጨዋቾቹ በሰሩበት ስራ ላይ ክፍያ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ገልጾ ውል አለን በማለት ብቻ ሳይሰሩ ደመወዝ ጠይቀዋል ያላቸውን የቢያድግልኝ ኤሊያስ ፣አብዱላዚዝ ተውፊቅ፣ አለማየሁ ሙለታ፣ሰለሞን ደምሴ፣ ፍጹም ገብረማርያም፣ ጌቱ ሃይለማሪያም፣ ምንተስኖት አሎና ዱሬሳ ሹቢሳ አቤቱታን ግን ውድቅ አድርጓል። ከዚህም በተጨማሪ ክለቡ ጥያቄያቸውን በተገቢነት ተቀብሎ እከፍላለሁ ያላቸውን የሃ/ሚካኤል አደፍርስና አንተነህ ተስፋዬን ክፍያና የተጨዋቾቹን አጠቃላይ የዘንድሮ ደመወዝ እስከ ሰኔ15/2014 ድረስ እንዲከፍል አዟል። በኮሚቴው ውሳኔ መሠረት ይግባኝ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ገልጾ ተጨዋቾቹ ግን በአስቸኳይ ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

በተባለው ቀን ካልተከፈለ የክፍያው አጠቃላይ መጠን ሁለት በመቶ በየዕለቱ እንዲከፍል፣ ከፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ግልጋሎት እንዳያገኝና ከውድድሩ እንዲታገድ ማዘዙን አስታውቋል። ሰበታ ከተማ ከፋሲል ከነማ ጋር የፊታችን ሃሙስ ከቀኑ 10 ሰአት ላይ ላለበት ጨዋታ ይደርሳሉ ወይ? የሚለው ጥያቄ አጓጊ ሆኗል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...