በእለቱ ከነበሩ ጨዋታዎች በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአለታ ወንዶ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጨዋታ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲዎች ባስቆጠሩት ብቸኛ የፍፁም ቅጣት ምት ጎል አንድ ለባዶ አሸንፈዋል።
በጨዋታው በርካታ ሙከራዎችን የተመለከትን ሲሆን አለታ ወንዶዎች አብዛኛውን የጨዋታ ጊዜ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሜዳ ክፍል አሳልፈዋል።

አለታ ወንዶዎች በቀኝ መስመር በሚጫወተው ጎሳዬ አማካኝነት በተደጋጋሚ ጥሩ ክሮሶችን ቢያገኙም መጠቀም አልቻሉም።
- ማሰታውቂያ -
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲዎች አብዛኛውን ኳስ በግራ መስመር በሚያጠቃው አቤሴሎም አፈወርቅ ለመጠቀም ሞክረዋል ።በመጨራሻም ጥረታቸው ሰምሮ ያገኙትን ፍፁም ቅጣት ምት አቤሴሎም አፈወርቅ አስቆጥሯል።
ከጎሏ በኋላ አለታ ወንዶዎች ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ጎል ማስቆጠር ግን አልቻሉም ።ጨዋታውም በአዲስ አበባ አንድ ለዜሮ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።
አጠቃላይ የዛሬ ውጤቶች
እሁድ ሐምሌ 18 ቀን 2013
ምድብ ለ
አሊ ሀብቴ ጋራዥ 3-1 አሳይታ ወረዳ
ሀዋሳ ዩንቨርስቲ ስታድየም
ምድብ ለ
ዳንቦያ ወረዳ 1-3 ወንዶ ገነት
ሀዋሳ ዩንቨርስቲ ስታድየም
ምድብ ሐ
ገንደ ሸበል 0-0 ሰመራ ሎግያ
ሀዋሳ ዩንቨርስቲ ስታድየም
ምድብ ሐ
አቃቂ ማዞርያ 2-2 ቡሳከተማ
ሀዋሳ ዩንቨርስቲ ስታድየም
ምድብ መ
ሀረር ዩናይትድ 1-2 ቫርኔሮ ወረዳ 13
ሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ
ምድብ መ
ዐመያ ወረዳ 1-0 ቦንጋ መምህራን ኮሌጅ
ሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ
ምድብ ሠ
አለታ ወንዶ 0-1 አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ
ሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ
ምድብ ሠ
አዲስ ቅዳም 1-0 ገንደ ተስፋ
ሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ
ምድብ ረ
ቦሌ ክፍለ ከተማ 2-0 ድሬ 06 ቀበሌ
ሀዋሳ ደቡብ ኮሌጅ ሜዳ
ምድብ ረ
አምሓራ ሳይንት 1-1 ጋርዱራ ከተማ
ሀዋሳ ደቡብ ኮሌጅ ሜዳ



