የፊታችን ዕሁድ የትንሳኤ ዕለት የሚዘጋጀውን የፊፋ ሲሪየስ ካፕን በዳኝነት ለማገልገል ሁለት ዕንስት ኢትዮጵያዊያን ወደ ናይሮቢ ያቀናሉ።

በቅርቡ የወንዶች የፊፋ ሲሪየስ ካፕን በዋና ዳኝነት ኢንተርናሽናል ዳኞቹ ሀይማኖት አዳነ እና ሔኖክ አበበ በረዳት ዳኝነት ደግሞ ፋሲካ የኋላሸት እና ዘመኑ ሲሳዬነው በጥሩ ብቃት ሩዋንዳ ላይ የነበረው ውድድር መርተው መምጣታቸው የሚታወስ ሲሆን አሁን ደግሞ የትንሳኤ ዕለት መጋቢት 4 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት በኬኒያ ናይሮቢ እስከ አሁን አራት ሀገራት ማለትም አውስትራሊያ ፣ ህንድ ፣ ኬኒያ እና ማላዊ ይሳተፋሉ በተባለበት የፊፋ ሴቶች ሲሪየስ ካፕ ላይ በዳኝነት ለመምራት ሁለት ኢትዮጵያዊያን ሴት ዳኞች ወደ ቦታው ያመራሉ።
የ2017 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ኮከቧ አዲሷ ኢንተርናሽናል ዳኛ ዮርዳኖስ ሙሉጌታ እና ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛዋ ይልፋሸዋ አየለ በዳኝነት እንዲያገለግሉ ተመርጠው ከሰሞኑ ወደ ስፍራው ያመራሉ ከተለያዩ ሀገራት አንድ አንድ ዳኛ በተመረጠበት በዚህ ውድድር ላይ ሁለት ኢትዮጵያዊን ኮታውን እንዲያገኙ በማድረግ የኢንስትራክተር ሊዲያ ታፈሠ ጥረት ከፍ ያለ ስለመሆኑም ተሰምቷል።
አስተያየት ይስጡ